የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ለፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች ከ17 ዓመት በታች የታዳጊ ውድድር ከሳምንት በኋላ ይጀምራል፡፡ የታዳጊዎችን ውድድርን በጥራት ለመምራት ከፍተኛ ትኩረት የሰጠው የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ በውድድሩ ተሳታፊ በሚሆኑ ክለቦች ላይ አስፈላጊውን  የእድሜ ማጣራት በማከናወን ከሞላ ጎደል ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ  ለማወቅ ተችሏል፡፡ በውድድሩ ከ17 ዓመት በታች ቡድናቸውን የሚያሳትፉ የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች ለተጨዋቾቻቸው የተዘጋጀውን የእድሜ ማረጋገጫ ምርመራ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የህክምና ኮሚቴ የግምባር ፍተሻ እና በቴክኒክ ኮሚቴው ተጨማሪ ማረጋገጫ መሰረት አከናውነዋል፡፡  ከ17 ዓመት በታች የታዳጊዎች ውድድሩ የካቲት 22 እንደሚጀመር የገለፀው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ተሳታፊ ክለቦች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ጥሪ ያስተላለፈ ሲሆን ዘንድሮ ተሳታፊ የሆኑ ክለቦች ብዛት 9 እንደሆኑና ውድድድራቸውን በደቡብ እና በማዕከላዊ ዞኖች በመከፋፈል እንደሚያደርጉ አስታውቋል፡፡ በማዕከላዊ ዞን  ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ኢትዮጵያ ቡና፤ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ ደደቢት፤ መብራት ሃይልና ሙገር ሲምንቶ ሲመደቡ፤ በደቡብ ዞን ደግሞ አርባምንጭ ፤ ሲዳማ ቡና እና ሃዋሳ ከነማ ይገኛሉ፡፡
ከ17 ዓመት በታች ውድድሩ የተዘጋጀው በታዳጊዎች ላይ በመስራት የአገሪቱን እግር ኳስ እድገት በጠንካራ መሰረት ላይ ለመጣል ያስችላል ተብሎ ነው የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ ለውድድሩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ተተኪ ተጨዋቾችን ለብሄራዊ ቡድን ለማፍራት እንደሚንቀሳቀስ  ስፖርት አድማስ ያነጋገራቸው የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ የውድድር ዋና ስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተድላ ዳኛቸው ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ  የታዳጊዎችን ውድድር ለማካሄድ በፌደሬሽን በኩል እንቅስቃሴው ከተጀመረ ቢቆይም ተግባራዊነቱ አልተሳካም ነበር፡፡ በቀድሞ የፌደሬሽን ስራ አስፈፃሚ የሴቶች እግር ኳስ  ቡድኖችን ከማቋቋም ባሻገር የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች የታዳጊ ቡድኖች እንዲኖራቸውና ውድድር እንዲያካሂዱ ከስምምነት ላይ ተደርሶ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ተድላ ዳኛቸው፤ አሁን ያለው አዲስ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴም በወጣቶች ላይ መስራት ለእግር ኳሱ እድገት ወሳኝ አቅጣጫ ነው በማለት የታዳጊዎች ውድድሩን ተግባራዊ ለማድረግ መወሰኑን ይገልፃሉ፡፡
የእድሜ ማረጋገጫ ምርመራዎች
አንድ ክለብ የሀ 17 ቡድን ሲመሰርት ማሟላት ያለበት መስፈርቶች በእግር ኳስ ፌደሬሽኑ በኩል ተቀምጠዋል፡፡ የመጀመርያው የተጨዋቾች የእድሜ ገደብን ማሟላትና ማረጋገጥ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ክለቦች በዘመናዊ የህክምና ምርመራ በማከናወን በሚያቀርቡት ማስረጃ ብቻ ሳይሆን በፌዴሬሽኑ የህክምና ኮሚቴ በኩል በግምባር የተጨዋቾችን ተክለሰውነት በተለያዩ ዘዴዎች በመፈተሽ በሚካሄድ  ምርመራ  መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ አቶ ተድላ ዳኛቸው እንደሚያስረዱት ክለቦች በየትኛውም ዘመናዊ የህክምና ተቋም የኤምአርአይ ምርመራቸውን ካከናወኑ በኋላ የፌደሬሽኑ  የቴክኒክ እና የህክምና ኮሚቴዎችን ተጨማሪ ማረጋገጫ ማድረግ ነበረባቸው፡፡ እንደ አቶ ተድላ ዳኛቸው ገለፃ ከኤምአርአይ ምርመራው ሌላ ኮሚቴዎቹ  በተለያዩ መንገዶች የተጨዋቾችን እድሜ ለማጣራት የሰሩት አንዳንድ የማጭበርበር ሁኔታዎችን ለማስቀረትነው፡፡ በዚህም መሰረት የህክምና ኮሚቴው የእያንዳንዱን ክለብ ተጨዋቾች  ወደ ስታድዬም ጠርቶ በአጠቃላይ ተክለሰውነታቸውን ገምግሟል፡፡ ማንኛውም ተጨዋች በሁሉም  ምርመራዎች የእድሜው ትክክለኛነት ካላረጋገጠ መጫወት አይችልም፡፡ ከ17 ዓመት በታች በተዘጋጀው የታዳጊዎች ውድድር ላይ የሚሳተፉ ክለቦች በስብስባቸው የሚይዟቸው ተጨዋቾች እድሜያቸው 15 እና 16 ዓመት  መሆን ሲገባው ይህን የእድሜ ገደብ በሟሟላት እስከ 25 ተጨዋቾች ያስመዘግባሉ፡፡  ክለቦች ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት የያዟቸውን ተጨዋቾች እድሜ በሁሉም ምርመራዎች እንዲያረጋግጡ በቂ ጊዜ ተሰጥቷቸው ነበር፡፡ እስከ የካቲት 15  የተሰጠው ቀነ ገደብ ዛሬ ያልቃል፡፡ ከዛሬ በፊት ብዙዎቹ ክለቦች የምርመራ ሂደቱን እንዳጠናቀቁ የሚናገሩት አቶ ተድላ፤ አንዳንድ ክለቦች ቢዘገዩም  በአስቸኳይ አስፈላጊውን መመርያ ተከትለው እንዲሰሩ በማበረታት ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት የማጣራት ሂደቱን እንዲጨርሱ ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል፡፡ በማዕከላዊ ዞን ካሉት ክለቦች ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ደደቢት፤ መከላከያ፤ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሉንም መስፈርቶች በሟሟላት እና በማረጋገጥ  የውድድሩን መጀመር በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡ አርባምንጭ ከነማ እና ሃዋሳ ከነማ ግን ትንሽ ቢዘገዩም በቀጣይ ሳምንት የምርመራውን ሂደት እንደሚጨርሱ ተስፋ ተደርጓል፡፡
የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ ከምንጊዜውም በላይ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ያለውን የእድሜ ማጭበርበር ችግር ለመፍታት ቁርጠኛ አቋም መያዙን የገለፁት የውድድር ዋና የስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተድላ ዳኛቸው፤ የተጨዋቾች መረጃ  በትክክለኛ መንገድ  ተሰርቶ በዘመናዊ የመረጃ ክምችት  መቀመጥ  ስላለበት የምርመራ ሂደቶችን በትኩረት መከናወናቸውን ያስረዳሉ፡፡ ከታዳጊዎች ውድድሩ ጋር በተያያዘ የተጨዋቾች ምዝገባ የተከናወነው አለም አቀፍ መመርያን በመከተል ነው፡፡ በዚህ መሰረትም በእግር ኳስ ፌደሬሽኑ አሰራር በትክክለኛ ምርመራዎች እድሜው ተረጋግጦ የተመዘገበ ተጨዋች ወደፊት እድሜውን ሊጨምር ወይንም ሊቀንስ የማይቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡
የውድድሩ አካሄድ እና ጠቀሜታዎች
ከ17 ዓመት በታች የሚካሄደው የታዳጊዎች ውድድር በአንድ ዙር እንደሚደረግ የተናገሩት የውድድር ዋና የስራ ሂደት ሃላፊው፤ የየክለቦቹ ተጨዋቾች ተማሪዎች እንደመሆናቸው ከውድድሩ በተያያዘ ትምህርታቸውን እንዳያስተጓጉልባቸው በሳምንት አንዴ ጨዋታዎችን ለማካሄድ እንደተወሰነና ታዳጊዎቹ በየስታድዬሞቹ በቂ ተመልካች እንዲያገኙ  ከተለያዩ የፕሪሚዬር ሊግና ሌሎች ውድድሮች ጋር ጎን ለጎን በማካሄድ  የፉክክር መንፈሱን ለማሟሟቅ መታሰቡን ገልፀዋል፡፡ በታዳጊዎች ውድድሩ ለሚያሸንፍ ክለብ ልዩ ዋንጫ መዘጋጀቱ እንደማይቀር የጠቀሱት የውድድር ዋና የስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተድላ ዳኛቸው፤ በታዳጊ ደረጃ የሚደረግ ውድድርን በተለያየ የማበረታቻ ድጋፎች ማስኬድ መሰረታዊ ጥቅም ስለሚኖረው የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ በዚህ ረገድ ትኩረት እንደሚሰጥ አስባለሁ ብለዋል፡፡
የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች በታዳጊዎች ውድድር በመሳተፋቸው በርካታ ጥቅሞችን እንደሚያገኙ የውድድር ዋና የስራ ሂደት ሃላፊው ያስገነዝባሉ፡፡ የመጀመርያው  ጥቅም ውድድሩ ለዋና ቡድናቸው በቂ እና ብቁ ተተኪ ተጨዋቾችን የሚያሳድጉበት እድል ለክለቦች ይፈጠርላቸዋል፡፡ ዋና ቡድናቸውን ለማጠናከር ብቻ ሳይሆን ክለቦች በተጨዋቾች የዝውውር ገበያ ከፍተኛ ወጪ የሚያወጡበትንም ሁኔታ የሚያስቀርና ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች ክለቦች ወጣት ተጨዋቾችን በዝውውር ገበያ በማቅረብ ገቢ ሊያገኙበት ይችላሉ፡፡ ከክለቦች ተጠቃሚነት ባሻገር ከፍተኛው ውጤት ክለቦች ለብሄራዊ ቡድን ወጣት እና ተተኪ ተጨዋቾችን በየጊዜው እንዲያፈሩ የሚያስችል መሆኑ ነው፡፡  በ2015 እኤአ ኒጀር ላይ በሚደረገው የአፍሪካ የሀ-17 ሻምፒዮና ኢትዮጵያ እንደምትሳተፍ አያይዘው ያነሱት አቶ ተድላ ዳኛቸው፤  በዚህ አህጉራዊ ሻምፒዮና ለሚሳተፈው የኢትዮጵያ ሀ 17 ብሄራዊ ቡድን የሚበቁ ተጨዋቾችን ለማግኘት ውድድሩ አመቺ መድረክ ይሆናል ብለዋል፡፡
በውድድሩ  ክለቦች በዋናነት በስልጠና ወጥ አሰራር እንዲኖራቸው ይደረጋል ያሉት  አቶ ተድላ ዳኛቸው፤  በየክለቡ ታዳጊዎችን የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች ብቃታቸው እንደሚመዘን ወጥ የሆነ የስልጠና መመርያ ተከትለው እንዲሰሩ እና እንዲወዳደሩ ጥረት እንደሚደረግ አስገንዝበው፤ ለዚህም  የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የቴክኒክ ዲፓርትመንት የስልጠና ማንዋል በመስራትና አሰልጣኞች ብቃታቸውን የሚያሳድጉባቸው ሴሚናሮች በማዘጋጀት እንደሚንቀሳቀስ በመግለፅም ታዳጊዎች  በወጥ  የስልጠና ሂደት በማለፍ ለብሄራዊ ቡድን ደረጃ ሲደርሱ በተመሳሳይ ብቃት እና አቋም እንዲኖራቸው ያስችላል ብለዋል፡፡
በክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬት ያለው ወቅታዊ ሁኔታ
ከ17 ዓመት በታች በሚደረገው የታዳጊዎች ውድድር ላይ ክለቦች ቡድኖችን በማቋቋም መሳተፋቸው በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽንን የሚጠየቀውን የአንድ እግር ኳስ ክለብ መመዘኛ ለሟሟላት ወሳኝ መሆኑን የሚገልፁት የውድድር ዋና የስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተድላ ዳኛቸው፤  የክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬትን በየደረጃው በማግኘት በአህጉራዊ ውድድሮች ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን  ያስረዳሉ፡፡ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን በወጣ መመርያ መሰረት አንድ ክለብ በውድድር ሲሳተፍ ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶች አሉ፡፡ እነዚህን መስፈርቶች የአፍሪካ እግር ኳስ ፌደሬሽን ያወጣው ያለምክንያት አይደለም፡፡ በሚያዘጋጃቸው አህጉራዊ ውድድሮች ለክለቦች የመሳተፍ ፍቃድ የሚሰጠው ተገቢውን መስፈርት አሟልተው የክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬት ያገኙትን ብቻ  ነው፡፡  ክለቦች ይሄው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን መመርያ ተገልጾላቸው የተቀመጡትን መመዘኛ መስፈርቶች እንዲያሟሉ ከተነገራቸው ሶስተ ዓመታት አልፈዋል፡፡ ከመስፈርቶቹ መካከል በቅድሚያ ክለቦች በአደረጃጀታቸው በወጣቶች ላይ የተመሰረት መዋቅር  እንዲኖራቸው ያስፈልጋል፤ ይህም የእግር ኳሱን ወጥ እድገት ለመቀጠል ወሳኝ ስለሆነ ነው፡፡
ክለቦች በታዳጊዎች እና በወጣቶች ስልጠና ሊያሰሯቸው የሚችሏቸው ብቁ አሰልጣኞች እንዲኖሯቸው ይጠየቃል፡፡ አንድ በፕሪሚዬር ሊግ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ ክለብ ክለብ የተሟላ ዕህፈት ቤት፤ በቂ የፋይናንሻል አቅም ፤ የስፖርት ማዘውተርያ ስፍራ፤ የተሟላ የባለሙያዎች አደረጃጀት ሊኖረው ይገባል፡፡ በእነዚህ መስፈርቶች መሰረት ክለቦች  በሶስት  ደረጃዎች በኤ፤ ቢ እና ሲ በመመዘን የህጋዊነት ሰርተፍኬት ይሰጣቸዋል፡፡ የህጋዊነት ሰርተፍኬቱን ለመስጠት የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ የክለቦች አደረጃጀት፤ አቅም አቅም በግንባር እንዲገመግም ሃላፊነት እንደተሰጠው አቶ ተድላ ዳኛቸው ሲናገሩ፤ ለዚህም ተብሎ ሁለት ኮሚቴዎች ተቋቁመው ከአዲሱ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጋር በመተዋወቅ በቅርቡ ስራቸውን ይጀምራሉ ብለዋል፡፡ በክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬት አሰጣጥ ላይ የሚሰሩት ኮሚቴዎች አንደኛው ቅደመ ውሳኔ የሚሰጥ ሲሆን ሌላኛው የይግባኝ ሰሚ  ነው፡፡ ቅድመ ውሳኔ የሚሰጠው ኮሚቴ በመጀመርያ ውሳኔ ሰጭነቱ ክለቡ ምን አሟልታል በሚል በቂ ግምገማ እና ክትትል በማድረግ የየክለቡን የፍቃድ ደረጃ የሚወስን ይሆናል፡፡ የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴው ደግሞ ክለቦች በቅድመ ውሳኔ ሰጪ ኮሚቴው በተሰጣቸው  ደረጃ ላይ ቅሬታ ካላቸው ይግባኝ ብለው የተሰጣቸውን ምዘና ሊያስተካክሉ የሚችሉበት ነው፡፡
አንዳንድ ሁኔታዎችን በመገንዘብ ለመረዳት እንደሚቻለው በክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬት መመዘኛ ብዙዎቹ  የኢትዮጵያ ክለቦች በሲ ደረጃ ሲሆኑ በቢ ደረጃ ያሉ ጥቂት ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ እግር ኳስ በኤ ደረጃ ሰርተፍኬት የሚያገኝ ክለብ የለም፡፡ በክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬት እንዲሰጥ መመርያ ያስፈለገው አንድ ክለብ በአህጉራዊ ደረጃ በሚደረጉ ውድድሮች ለመሳተፍ ማሟሟላት  የሚገባው ደረጃዎች ስላሉ ነው፡፡ ክለቦች በዚህ መመርያ መሰረት ሊያሟሉ የሚገባቸውን መስፈርቶች እንዲያሟሉ በፊፋ በኩል የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በተደጋጋሚ ቢሰጡም ብዙም እየተራመዱ አይደለም፡፡  የፐሪሚዬር ሊግ  ክለቦች አስቀድመው የሴቶች ቡድን በማቋቋም ተንቀሳቀሰው አሁን ውድድር እየተደረገ ውጤቱን በማየት ላይ ናቸው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የሀ 17 ቡድኖች መያዛቸው አንዱ ርምጃ ሲሆን አንዳንድ ክለቦች የቴክኒክ ዲያሬክተር መቅጠራቸው፤ በማርኬቲንግ ባለሙያ መስራትም መጀመራቸውም እንደለውጥ የሚታይ ቢሆንም ገና ብዙ መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡

        የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ለፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች ከ17 ዓመት በታች የታዳጊ ውድድር ከሳምንት በኋላ ይጀምራል፡፡ የታዳጊዎችን ውድድርን በጥራት ለመምራት ከፍተኛ ትኩረት የሰጠው የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ በውድድሩ ተሳታፊ በሚሆኑ ክለቦች ላይ አስፈላጊውን  የእድሜ ማጣራት በማከናወን ከሞላ ጎደል ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ  ለማወቅ ተችሏል፡፡ በውድድሩ ከ17 ዓመት በታች ቡድናቸውን የሚያሳትፉ የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች ለተጨዋቾቻቸው የተዘጋጀውን የእድሜ ማረጋገጫ ምርመራ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የህክምና ኮሚቴ የግምባር ፍተሻ እና በቴክኒክ ኮሚቴው ተጨማሪ ማረጋገጫ መሰረት አከናውነዋል፡፡  ከ17 ዓመት በታች የታዳጊዎች ውድድሩ የካቲት 22 እንደሚጀመር የገለፀው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ተሳታፊ ክለቦች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ጥሪ ያስተላለፈ ሲሆን ዘንድሮ ተሳታፊ የሆኑ ክለቦች ብዛት 9 እንደሆኑና ውድድድራቸውን በደቡብ እና በማዕከላዊ ዞኖች በመከፋፈል እንደሚያደርጉ አስታውቋል፡፡ በማዕከላዊ ዞን  ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ኢትዮጵያ ቡና፤ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ ደደቢት፤ መብራት ሃይልና ሙገር ሲምንቶ ሲመደቡ፤ በደቡብ ዞን ደግሞ አርባምንጭ ፤ ሲዳማ ቡና እና ሃዋሳ ከነማ ይገኛሉ፡፡
ከ17 ዓመት በታች ውድድሩ የተዘጋጀው በታዳጊዎች ላይ በመስራት የአገሪቱን እግር ኳስ እድገት በጠንካራ መሰረት ላይ ለመጣል ያስችላል ተብሎ ነው የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ ለውድድሩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ተተኪ ተጨዋቾችን ለብሄራዊ ቡድን ለማፍራት እንደሚንቀሳቀስ  ስፖርት አድማስ ያነጋገራቸው የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ የውድድር ዋና ስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተድላ ዳኛቸው ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ  የታዳጊዎችን ውድድር ለማካሄድ በፌደሬሽን በኩል እንቅስቃሴው ከተጀመረ ቢቆይም ተግባራዊነቱ አልተሳካም ነበር፡፡ በቀድሞ የፌደሬሽን ስራ አስፈፃሚ የሴቶች እግር ኳስ  ቡድኖችን ከማቋቋም ባሻገር የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች የታዳጊ ቡድኖች እንዲኖራቸውና ውድድር እንዲያካሂዱ ከስምምነት ላይ ተደርሶ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ተድላ ዳኛቸው፤ አሁን ያለው አዲስ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴም በወጣቶች ላይ መስራት ለእግር ኳሱ እድገት ወሳኝ አቅጣጫ ነው በማለት የታዳጊዎች ውድድሩን ተግባራዊ ለማድረግ መወሰኑን ይገልፃሉ፡፡
የእድሜ ማረጋገጫ ምርመራዎች
አንድ ክለብ የሀ 17 ቡድን ሲመሰርት ማሟላት ያለበት መስፈርቶች በእግር ኳስ ፌደሬሽኑ በኩል ተቀምጠዋል፡፡ የመጀመርያው የተጨዋቾች የእድሜ ገደብን ማሟላትና ማረጋገጥ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ክለቦች በዘመናዊ የህክምና ምርመራ በማከናወን በሚያቀርቡት ማስረጃ ብቻ ሳይሆን በፌዴሬሽኑ የህክምና ኮሚቴ በኩል በግምባር የተጨዋቾችን ተክለሰውነት በተለያዩ ዘዴዎች በመፈተሽ በሚካሄድ  ምርመራ  መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ አቶ ተድላ ዳኛቸው እንደሚያስረዱት ክለቦች በየትኛውም ዘመናዊ የህክምና ተቋም የኤምአርአይ ምርመራቸውን ካከናወኑ በኋላ የፌደሬሽኑ  የቴክኒክ እና የህክምና ኮሚቴዎችን ተጨማሪ ማረጋገጫ ማድረግ ነበረባቸው፡፡ እንደ አቶ ተድላ ዳኛቸው ገለፃ ከኤምአርአይ ምርመራው ሌላ ኮሚቴዎቹ  በተለያዩ መንገዶች የተጨዋቾችን እድሜ ለማጣራት የሰሩት አንዳንድ የማጭበርበር ሁኔታዎችን ለማስቀረትነው፡፡ በዚህም መሰረት የህክምና ኮሚቴው የእያንዳንዱን ክለብ ተጨዋቾች  ወደ ስታድዬም ጠርቶ በአጠቃላይ ተክለሰውነታቸውን ገምግሟል፡፡ ማንኛውም ተጨዋች በሁሉም  ምርመራዎች የእድሜው ትክክለኛነት ካላረጋገጠ መጫወት አይችልም፡፡ ከ17 ዓመት በታች በተዘጋጀው የታዳጊዎች ውድድር ላይ የሚሳተፉ ክለቦች በስብስባቸው የሚይዟቸው ተጨዋቾች እድሜያቸው 15 እና 16 ዓመት  መሆን ሲገባው ይህን የእድሜ ገደብ በሟሟላት እስከ 25 ተጨዋቾች ያስመዘግባሉ፡፡  ክለቦች ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት የያዟቸውን ተጨዋቾች እድሜ በሁሉም ምርመራዎች እንዲያረጋግጡ በቂ ጊዜ ተሰጥቷቸው ነበር፡፡ እስከ የካቲት 15  የተሰጠው ቀነ ገደብ ዛሬ ያልቃል፡፡ ከዛሬ በፊት ብዙዎቹ ክለቦች የምርመራ ሂደቱን እንዳጠናቀቁ የሚናገሩት አቶ ተድላ፤ አንዳንድ ክለቦች ቢዘገዩም  በአስቸኳይ አስፈላጊውን መመርያ ተከትለው እንዲሰሩ በማበረታት ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት የማጣራት ሂደቱን እንዲጨርሱ ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል፡፡ በማዕከላዊ ዞን ካሉት ክለቦች ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ደደቢት፤ መከላከያ፤ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሉንም መስፈርቶች በሟሟላት እና በማረጋገጥ  የውድድሩን መጀመር በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡ አርባምንጭ ከነማ እና ሃዋሳ ከነማ ግን ትንሽ ቢዘገዩም በቀጣይ ሳምንት የምርመራውን ሂደት እንደሚጨርሱ ተስፋ ተደርጓል፡፡
የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ ከምንጊዜውም በላይ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ያለውን የእድሜ ማጭበርበር ችግር ለመፍታት ቁርጠኛ አቋም መያዙን የገለፁት የውድድር ዋና የስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተድላ ዳኛቸው፤ የተጨዋቾች መረጃ  በትክክለኛ መንገድ  ተሰርቶ በዘመናዊ የመረጃ ክምችት  መቀመጥ  ስላለበት የምርመራ ሂደቶችን በትኩረት መከናወናቸውን ያስረዳሉ፡፡ ከታዳጊዎች ውድድሩ ጋር በተያያዘ የተጨዋቾች ምዝገባ የተከናወነው አለም አቀፍ መመርያን በመከተል ነው፡፡ በዚህ መሰረትም በእግር ኳስ ፌደሬሽኑ አሰራር በትክክለኛ ምርመራዎች እድሜው ተረጋግጦ የተመዘገበ ተጨዋች ወደፊት እድሜውን ሊጨምር ወይንም ሊቀንስ የማይቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡
የውድድሩ አካሄድ እና ጠቀሜታዎች
ከ17 ዓመት በታች የሚካሄደው የታዳጊዎች ውድድር በአንድ ዙር እንደሚደረግ የተናገሩት የውድድር ዋና የስራ ሂደት ሃላፊው፤ የየክለቦቹ ተጨዋቾች ተማሪዎች እንደመሆናቸው ከውድድሩ በተያያዘ ትምህርታቸውን እንዳያስተጓጉልባቸው በሳምንት አንዴ ጨዋታዎችን ለማካሄድ እንደተወሰነና ታዳጊዎቹ በየስታድዬሞቹ በቂ ተመልካች እንዲያገኙ  ከተለያዩ የፕሪሚዬር ሊግና ሌሎች ውድድሮች ጋር ጎን ለጎን በማካሄድ  የፉክክር መንፈሱን ለማሟሟቅ መታሰቡን ገልፀዋል፡፡ በታዳጊዎች ውድድሩ ለሚያሸንፍ ክለብ ልዩ ዋንጫ መዘጋጀቱ እንደማይቀር የጠቀሱት የውድድር ዋና የስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተድላ ዳኛቸው፤ በታዳጊ ደረጃ የሚደረግ ውድድርን በተለያየ የማበረታቻ ድጋፎች ማስኬድ መሰረታዊ ጥቅም ስለሚኖረው የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ በዚህ ረገድ ትኩረት እንደሚሰጥ አስባለሁ ብለዋል፡፡
የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች በታዳጊዎች ውድድር በመሳተፋቸው በርካታ ጥቅሞችን እንደሚያገኙ የውድድር ዋና የስራ ሂደት ሃላፊው ያስገነዝባሉ፡፡ የመጀመርያው  ጥቅም ውድድሩ ለዋና ቡድናቸው በቂ እና ብቁ ተተኪ ተጨዋቾችን የሚያሳድጉበት እድል ለክለቦች ይፈጠርላቸዋል፡፡ ዋና ቡድናቸውን ለማጠናከር ብቻ ሳይሆን ክለቦች በተጨዋቾች የዝውውር ገበያ ከፍተኛ ወጪ የሚያወጡበትንም ሁኔታ የሚያስቀርና ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች ክለቦች ወጣት ተጨዋቾችን በዝውውር ገበያ በማቅረብ ገቢ ሊያገኙበት ይችላሉ፡፡ ከክለቦች ተጠቃሚነት ባሻገር ከፍተኛው ውጤት ክለቦች ለብሄራዊ ቡድን ወጣት እና ተተኪ ተጨዋቾችን በየጊዜው እንዲያፈሩ የሚያስችል መሆኑ ነው፡፡  በ2015 እኤአ ኒጀር ላይ በሚደረገው የአፍሪካ የሀ-17 ሻምፒዮና ኢትዮጵያ እንደምትሳተፍ አያይዘው ያነሱት አቶ ተድላ ዳኛቸው፤  በዚህ አህጉራዊ ሻምፒዮና ለሚሳተፈው የኢትዮጵያ ሀ 17 ብሄራዊ ቡድን የሚበቁ ተጨዋቾችን ለማግኘት ውድድሩ አመቺ መድረክ ይሆናል ብለዋል፡፡
በውድድሩ  ክለቦች በዋናነት በስልጠና ወጥ አሰራር እንዲኖራቸው ይደረጋል ያሉት  አቶ ተድላ ዳኛቸው፤  በየክለቡ ታዳጊዎችን የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች ብቃታቸው እንደሚመዘን ወጥ የሆነ የስልጠና መመርያ ተከትለው እንዲሰሩ እና እንዲወዳደሩ ጥረት እንደሚደረግ አስገንዝበው፤ ለዚህም  የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የቴክኒክ ዲፓርትመንት የስልጠና ማንዋል በመስራትና አሰልጣኞች ብቃታቸውን የሚያሳድጉባቸው ሴሚናሮች በማዘጋጀት እንደሚንቀሳቀስ በመግለፅም ታዳጊዎች  በወጥ  የስልጠና ሂደት በማለፍ ለብሄራዊ ቡድን ደረጃ ሲደርሱ በተመሳሳይ ብቃት እና አቋም እንዲኖራቸው ያስችላል ብለዋል፡፡
በክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬት ያለው ወቅታዊ ሁኔታ
ከ17 ዓመት በታች በሚደረገው የታዳጊዎች ውድድር ላይ ክለቦች ቡድኖችን በማቋቋም መሳተፋቸው በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽንን የሚጠየቀውን የአንድ እግር ኳስ ክለብ መመዘኛ ለሟሟላት ወሳኝ መሆኑን የሚገልፁት የውድድር ዋና የስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተድላ ዳኛቸው፤  የክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬትን በየደረጃው በማግኘት በአህጉራዊ ውድድሮች ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን  ያስረዳሉ፡፡ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን በወጣ መመርያ መሰረት አንድ ክለብ በውድድር ሲሳተፍ ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶች አሉ፡፡ እነዚህን መስፈርቶች የአፍሪካ እግር ኳስ ፌደሬሽን ያወጣው ያለምክንያት አይደለም፡፡ በሚያዘጋጃቸው አህጉራዊ ውድድሮች ለክለቦች የመሳተፍ ፍቃድ የሚሰጠው ተገቢውን መስፈርት አሟልተው የክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬት ያገኙትን ብቻ  ነው፡፡  ክለቦች ይሄው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን መመርያ ተገልጾላቸው የተቀመጡትን መመዘኛ መስፈርቶች እንዲያሟሉ ከተነገራቸው ሶስተ ዓመታት አልፈዋል፡፡ ከመስፈርቶቹ መካከል በቅድሚያ ክለቦች በአደረጃጀታቸው በወጣቶች ላይ የተመሰረት መዋቅር  እንዲኖራቸው ያስፈልጋል፤ ይህም የእግር ኳሱን ወጥ እድገት ለመቀጠል ወሳኝ ስለሆነ ነው፡፡
ክለቦች በታዳጊዎች እና በወጣቶች ስልጠና ሊያሰሯቸው የሚችሏቸው ብቁ አሰልጣኞች እንዲኖሯቸው ይጠየቃል፡፡ አንድ በፕሪሚዬር ሊግ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ ክለብ ክለብ የተሟላ ዕህፈት ቤት፤ በቂ የፋይናንሻል አቅም ፤ የስፖርት ማዘውተርያ ስፍራ፤ የተሟላ የባለሙያዎች አደረጃጀት ሊኖረው ይገባል፡፡ በእነዚህ መስፈርቶች መሰረት ክለቦች  በሶስት  ደረጃዎች በኤ፤ ቢ እና ሲ በመመዘን የህጋዊነት ሰርተፍኬት ይሰጣቸዋል፡፡ የህጋዊነት ሰርተፍኬቱን ለመስጠት የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ የክለቦች አደረጃጀት፤ አቅም አቅም በግንባር እንዲገመግም ሃላፊነት እንደተሰጠው አቶ ተድላ ዳኛቸው ሲናገሩ፤ ለዚህም ተብሎ ሁለት ኮሚቴዎች ተቋቁመው ከአዲሱ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጋር በመተዋወቅ በቅርቡ ስራቸውን ይጀምራሉ ብለዋል፡፡ በክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬት አሰጣጥ ላይ የሚሰሩት ኮሚቴዎች አንደኛው ቅደመ ውሳኔ የሚሰጥ ሲሆን ሌላኛው የይግባኝ ሰሚ  ነው፡፡ ቅድመ ውሳኔ የሚሰጠው ኮሚቴ በመጀመርያ ውሳኔ ሰጭነቱ ክለቡ ምን አሟልታል በሚል በቂ ግምገማ እና ክትትል በማድረግ የየክለቡን የፍቃድ ደረጃ የሚወስን ይሆናል፡፡ የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴው ደግሞ ክለቦች በቅድመ ውሳኔ ሰጪ ኮሚቴው በተሰጣቸው  ደረጃ ላይ ቅሬታ ካላቸው ይግባኝ ብለው የተሰጣቸውን ምዘና ሊያስተካክሉ የሚችሉበት ነው፡፡
አንዳንድ ሁኔታዎችን በመገንዘብ ለመረዳት እንደሚቻለው በክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬት መመዘኛ ብዙዎቹ  የኢትዮጵያ ክለቦች በሲ ደረጃ ሲሆኑ በቢ ደረጃ ያሉ ጥቂት ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ እግር ኳስ በኤ ደረጃ ሰርተፍኬት የሚያገኝ ክለብ የለም፡፡ በክለቦች ህጋዊነት ሰርተፍኬት እንዲሰጥ መመርያ ያስፈለገው አንድ ክለብ በአህጉራዊ ደረጃ በሚደረጉ ውድድሮች ለመሳተፍ ማሟሟላት  የሚገባው ደረጃዎች ስላሉ ነው፡፡ ክለቦች በዚህ መመርያ መሰረት ሊያሟሉ የሚገባቸውን መስፈርቶች እንዲያሟሉ በፊፋ በኩል የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በተደጋጋሚ ቢሰጡም ብዙም እየተራመዱ አይደለም፡፡  የፐሪሚዬር ሊግ  ክለቦች አስቀድመው የሴቶች ቡድን በማቋቋም ተንቀሳቀሰው አሁን ውድድር እየተደረገ ውጤቱን በማየት ላይ ናቸው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የሀ 17 ቡድኖች መያዛቸው አንዱ ርምጃ ሲሆን አንዳንድ ክለቦች የቴክኒክ ዲያሬክተር መቅጠራቸው፤ በማርኬቲንግ ባለሙያ መስራትም መጀመራቸውም እንደለውጥ የሚታይ ቢሆንም ገና ብዙ መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡

           በ2014 የአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ የአምናው የፕሪሚዬር ሊግ ሻምፒዮን ደደቢት ወደ አንደኛ ዙር ማጣርያ ማለፉን አረጋገጠ፡፡ በሌላ በኩል በ2014 የአፍሪካ ክለቦች ኮንፌደሬሽን ካፕ  ቅድመ ማጣሪያ በሁለቱም ጨዋታ የተሸነፈው መከላከያ ከውድድሩ ውጭ ሆኗል። ባለፈው ሰሞን በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ የቅድመ ማጣርያ የመልስ ጨዋታ  ደደቢት ከሜዳው ውጭ በዛንዚባሩ ኬኤምኬኤም 2ለ0 ቢሸነፍም፤ በአጠቃላይ የደርሶ መልስ ውጤት 3ለ2 አሸንፏል።  በኮንፌደሬሽን ካፕ ቅድመ መጣርያ የመልስ ጨዋታ ሊዮፓርድስን በሜዳው ያስተናገደው የአምናው የጥሎ ማለፍ ሻምፒዮን መከላከያ 2ለ0 ተሸንፎ በአጠቃላይ ውጤት 4ለ0 ተረትቶ ከውድድሩ ተሰናብቷል፡፡ በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ አንደኛ ዙር የማጣርያ ምእራፍ ኢትዮጵያን የወከለው ደደቢት የሚገናኘው  ከቱኒዚያው ክለብ ሲኤስ ሴፋክሲዬን ጋር ነው፡፡ ደደቢት ከቱኒዚያው ክለብ ጋር የደርሶ መልስ ትንቅንቁን ከሳምንት በኋላ በሜዳው ይጀምራል፡፡  
መከላከያ ትኩረቱን ወደ ሊጉ ይመልሳል
በ2014 የአፍሪካ ክለቦች ኮንፌደሬሽን ካፕ የቅድመ ማጣርያ የመልስ ጨዋታዎች ወደ አንደኛ ዙር ለመግባት 11 ክለቦች እድል ነበራቸው፡፡ ባለፈው የውድድር ዘመን የጥሎ ማለፍ አሸናፊ የነበረው መከላከያ ከታላቁ የኬንያ ክለብ ጋር በመደልደሉ ቅድመ ማጣርያውን ማለፍ አልቻለም፡፡ መከላከያ ትኩረቱን ወደ ፕሪሚዬር ሊጉ በመመለስ ለዋንጫ ተፎካካሪ እንደሚሆን ተገምቷል። መከላከያ ከዘንድሮ በፊት በአፍሪካ ደረጃ በሁለት የውድድር ዘመናት የተሳትፎ ልምድ ነበረው፡፡ ለመጀመርያ ጊዜ ድሮ “ካፕዊነርስ ካፕ” ተብሎ በሚጠራው የጥሎ ማለፍ ዋንጫ በ1976 እኤአ ተሳትፏል፡፡ በወቅቱም እስከ ሩብ ፍፃሜ ለመጓዝ በቅቶ ነበር፡፡ በ2007 እኤአ ላይ ደግሞ በኮንፌደሬሽን ካፕ ሲሳተፍ ቅድመ ማጣርያውን አልፎ ነበር፡፡ ከዚያ በመጀመርያው ዙር ክለብ በሆነ የደርሶ መልስ ውጤት ተሸንፎ ከውድድሩ ውጭ ሆኗል፡፡
ደደቢት 3 ኬኤምኬኤም 2
በ2014 የአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ ከሳምንት በፊት በቅድመ ማጣርያ የመልስ ጨዋታዎች 14 ክለቦች ወደ አንደኛ ዙር ማጣርያ ማለፋቸውን አረጋግጠዋል፡፡ አምና የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግን በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሸነፈው ደደቢት በኢትዮጵያ የክለቦች ውድድር በአጭር ጊዜ ስኬታማ በመሆን ከመደነቁም በላይ ለዋናው ብሄራዊ ቡድን ባለው አስተዋፅኦም የተለየ ነው፡፡ በ2011 እና በ2012 እኤአ የጥሎ ማለፍ ሻምፒዮን ለመሆን የበቃው ደደቢት ለዚህ ውጤቱ በሁለት የውድድር ዘመን የአፍሪካ ክለቦች ኮንፌዴሬሽን ካፕን ለመሳተፍ ልምድ አለው፡፡ በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ ኢትየጵያን ሲወክል ግን ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡
በሻምፒዮንስ ሊጉ የመጀመሪያ ዙር ማጣርያ የደደቢት ተጋጣሚ የሆነው የቱኒዚያው ክለብ ሴፋክስዬን በስኬት እና በምርጥነት ከአፍሪካ 5 ታላላቅ ክለቦች ተርታ የሚሰለፍ ነው፡፡ የቱኒዚያ ፕሪሚዬር ሊግን ለ8 ጊዜ ያሸነፈው ሴፋክስዬን በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ሁለት ጊዜ በነበረው ተሳትፎ በ2006 ኤአ ላይ ሁለተኛ ደረጃ ያገኘበት ውጤት ከፍተኛው ነበር፡፡ በኮንፌደሬሽን ካፕ ደግሞ በ2007፤ በ2008 እና በ2013 እኤአ ለሶስት ጊዜያት ዋንጫውን በማንሳት እና በ2008 እና 20009 እኤአ በካፍ ሱፕር ካፕ ሁለተኛ ደረጃን አከታትሎ አስመዝግቧል፡፡
በቱኒዚያዊው አሰልጣኝ ሃመዲ ዳው የሚመራው ሴፋክሴዬን በተጨዋቾች ስብስቡ የካሜሮን፤ የጋና፤ የአይቬሪኮስት፤ የጋቦንና የሞሮኮ ተጨዋቾችን ያካተተ ሲሆን አጠቃላይ 26 ተጨዋቾች የሚገኙበት ስብስቡ በትራንስፈርማርኬት የዝውውር ገበያ ስሌት 8 ሚሊዮን 750ሺ ዩሮ የተተመነ ነው፡፡ 3152 የተመዘገቡ አባላት ያሉት ሴፋክሴዬን በሜዳነት የሚጠቀመወ 12ሺ ተመልካች የሚያስተናግደውን ስታዴ ታሌብ ማሃሪ ስታድዬምን    ነው፡፡

Saturday, 22 February 2014 13:21

ወንጀል

“ቨርጂኒያ “ጂንጀር” ላይትሌይ በቴክሳስ ምስራቃዊ ክፍል ኮሬይቪል ኮፊ ኬክስ በሚባል ስም የሚታወቀው በጣም ዝነኛ የኬክ መጋገሪያ ድርጅት ባለቤት ነች፡፡ የራሷ ፈጠራ ብቻ የሆነውን የኬክ ጣዕም ለመቅመስ ደንበኞቿ ከሩቅ ቦታ ወደ ትንሿ መደብር ይመጣሉ። አንድ ወጣት ልጅ ዝነኛ ኬኳን ከበላ በኋላ ከተማው ውስጥ ሞቶ ስለተገኘ ለመላው ማህበረሰብ እጅግ አስደንጋጭ ነገር ሆነ። በቅርቡ በኃላፊነት የተሾመው የፖሊስ አዛዥ ለጉዳዩ አስቸኳይ ዕልባት ለመስጠት ቃል ተብቷል፡፡ ጂንጀር ልትረዳው ብትፈልግም፣ እሱ ግን ድርጅቷ ውስጥ ተቀጣሪ የሆነን ሰው በግድያ ወንጀል ከሰሰ፡፡ እሷ ደግሞ ወጣቱ የፖሊስ አዛዥ ስለግድያ ወንጀሉ የደረሰበትን ድምዳሜ ስላለመነችበት ተቃወመችና ወንጀለኛውን ለማወቅ በምስጢር ራሷ ወንጀሉን መከታተል ጀመረች።”
ርዕስ- ጣፋጭ ጂንጀር መርዝ (Sweet Ginjer Poison)
ደራሲ - ሮበርት በርተን ሮቢንሰን
ተርጓሚ - አምሳሉ ጌታሁን ደርሰህ
ዋጋ 35 ብር
ህትመት - ላንጋኖ ማተሚያ ቤት

Saturday, 22 February 2014 13:19

ወግ

“አንድ ደራሲ በመግቢያው ስለ ጠቅላላ መፅሀፉ ይዘት ሲያብራራ ታላቅ ድግስ አዘጋጅቶ መግቢያ በሩ ላይ በመቆም ውስጥ ስለተዘጋጀው ምግብ ጣፋጭነት እየመሰከረ ወደ ብፌው አቅጣጫ እንደሚመራ ጋባዥ መሆኑ ነው፡፡
ደራሲውም ሆነ ጋባዡ መግቢያው ላይ ቆመው በአንድ አይነት ዜማ ታዳሚው ስለ ድግሱ በቂ ግንዛቤ ኖሮት እንዲገባ በማስረዳት ይደክማሉ፡፡ ይሄን ድግስ ለማዘጋጀት ስለ ተደከመው ድካም፣ በውጤቱም ስለተዘጋጁት አይነቶችም ያብራራሉ።
በውስጥ ስለተደገሰው ድግስ በራፍ ላይ ሆኖ የማብራራት አስፈላጊነት ወይም አላማ የታዳሚውን የመብላት ፍላጎት ማናር /አፒታይዘር/ ጭምር ሳይሆን አይቀርም፡፡ በእኔ እምነት ይህ ተግባር ተጋባዡን ጉጉ ያደርገዋል፡፡
በዚህ መፅሃፍ ውስጥ ስለተካተቱት ታሪኮች ይዘት ማውራት ካለብኝ ከአትኩሮታቸው በመነሳት እጀምራለሁ፡፡ በአንድ የማህበረሰብ ስብስብ ውስጥ (ሀገር ሊሆን ይችላል) ወሳኝ ሚና ስላላቸው፣ የየነዋሪውም ዋነኛ ግዱ ስለሆኑት ማለትም … ሀይማኖት፣ ፖለቲካና ማህበረ-ባህላዊ እሳቤ ለመዳሰስ ሞክሬያለሁ፡፡”  
ርዕስ - ሕዝብ እና ነፃነት
ደራሲ - ሚካኤል ዲኖ
ዋጋ - 44 ብር

Saturday, 22 February 2014 13:17

ሰሞኑን የወጡ መፃህፍት

ግጥም
“የሰረቀ ሌባ
በካቴና ታስሮ
በፖሊስ ተይዞ
ሲሄድ ወደ ጣቢያ
መንገድ ላይ ያይሃል
ሊሰርቅ የሚሄደው
ዕልፍ-አዕላፍ
ሌባ፡፡”
ርዕስ -
ሲጠይቁ መኖር
(የግጥም ስብሰባ)   
ደራሲ - ደረጀ ምንላርግህ
ዋጋ - 34ብር
ህትመት - አንድነት ፕሪንተርስ

Saturday, 22 February 2014 13:14

ከመሸ ብትመጡ …

“ለሜላት ያለህ ፍቅር ለማክዳ ካለህ ፍቅር እንደሚበልጥ ማቲማቲካል ሎጂክ በመጠቀም በፍጥነት አስረዳ” አለው አቃቤ ህጉ፤ ለተከሳሹ፡፡ ተከሳሹ አይኑን ጣራው ላይ ሰቅሎ መልስ ሲፈልግ ለቅፅበት ከቆየ በኋላ የሸመደደውን እንደሚለፈልፍ ተማሪ መንተባተብ ጀመረ፡፡
“X ኢዝ ኢኩዋል ቱ … እኔ ለእንግሊዝኛ ግጥም ያለኝ ፍቅር
“Y ኢዝ ኢኩዋል ቱ … እኔ ለማክዳ ያለኝ ፍቅር
ዜን - “X ኢዝ ግሬተር ዛን “Y”
ናው ሌት “Z” ቢ ኢኩዋል ቱ እኔ ለሜላት ያለኝ ፍቅር
ስለዚህ “Z” ከ “Y” መብለጡ እኔ ከምወደው ስራዬ ተባርሬ ለሜላት ስል መታሰሬ ግልፅ ስለሆነ
ዜር ፎር “Z” ኢዝ Greater than “X”
“በትክክል መልሰሀል፤ አሁን ወደ መስቀለኛው ጥያቄ እንሂድ” አለ አቃቤ ህጉ፤ ሞቅ ያለ ጭብጨባ ለተከሳሹ ከሰጠው በኋላ፡፡ ጥያቄውን በፍጥነት ሰረዘበት፡፡
“በሳጥን ነው ወይንስ በሰሌን መቀበር የምትፈልገው?”
“ባልቀበር እመርጣለሁ?” መለሰ ተከሳሹ፡፡
“መቀበርህማ አይቀርም! የተጠየቅኸውን ብቻ መልስ”
“በሰሌን ይሻለኛል”
“ለምን?”
“የሬሳ ሳጥን ውድ ነው፤ ሳጥኑን ከሞተ ሰው ጋር ከመቅበር በህይወት ያለ ሰው እንደ አልጋ ቢገለገልበት ይሻላል”
“መልካም … በአለም ላይ ስንት አልጋ እንዳለ ቁጥሩን አስልተህ ንገረኝ?”
“የአለምን ህዝብ ቁጥር የሚያክል አልጋ አለ፡፡ ስምንት ቢሊዮን አልጋ ማለት ነው፡፡ … ነገር ግን ሰው ሲሞት አልጋው አብሮት ስለማይቀበር፣ የአልጋው ቁጥር ሁሌ እያሻቀበ ይሄዳል” ብሎ ተከሳሹ በጉጉት የአቃቤ ህጉን ፊት ተመለከተ፡፡ አቃቤ ህጉ በመልሱ አልረካም፡፡
“ለምሳሌ አንተ አልጋ የለህም፤ አልጋህን የት እንዳደረስከው ተናገር፤ ገድለህ፣ ቆራርጠህ አልቀበርከውም?”
“እኔ አልጋዬን አልገደልኩትም … የመጠጥ ሂሳብ ክፈል እያለ ጋሽ ያሲን ሲያስፈራራኝ ለቆራሌው ሸጥኩት እንጂ አልጋዬን ገድዬ አልቀበርኩም…”
አቃቤ ህጉ፤ ድንገት ተበሳጭቶ ወደሱ ተንደረደረ፡፡ በጥፊ ይጠፈጥፈው ጀመር፡፡ ተጠፍጣፊው ለመጮህ ቢሞክርም ድምፁ አልወጣ አለው፡፡ ደግሞ ጥፊው እንደ አለንጋ በማጅራቱ ዞሮ የሚጠመጠም አይነት ነው፡፡ ጥፊው በጣም ይቀዘቅዛል፡፡
እያጓራ ባንኖ የነቃው ይኼኔ ነው፡፡ ፊቱ ላይ እየተጨፈጨ ያለውን የሚከረፋ ሽታ ያለውን መወልወያ ለመሸሽ ተኝቶበት ከነበረው ጥጥ ፍራሹ ደንብሮ በአራት እግሩ ዳኸ፡፡ ምን እየተከሰተ እንደሆነ ሊገባው አልቻለም፡፡
አይኑን በሚጭበረበረው ብርሐን እንደምንም ለመግለጥ ጣረ፡፡ የታላቅ ወንድሙን ሱሪ እና የጫማውን ጠረን አወቃቸው፡፡
ታላቅ ወንድሙ ከበላዩ ቆሟል “ምን አባክ ሆነህ ነው” አለ በሚንቀጠቀጥ ድምፅ፡፡ (ታላቅ ወንድሙ ቢሆንስ ለምንድነው በእርጥብ መወልወያ የሚገርፈው?)
የታላቅ ወንድሙን ሱሪ ጨምድዶ ለመቆም ሲሞክር ወደቀ፡፡ የታላቅ ወንድምየው ሱሪው እንዳይወልቅ …ያኛውን ሲጠፈጥፍ የነበረበትን የረጠበ ፎጣ ጥሎ በሁለት እጁ ቀበቶውን አፈፍ አድርጐ ያዘ፡፡
“ምን ፈልገህ ነው?” እያለ ታናሽየው፤ አሁንም ለመቆም በመንደፋደፍ ላይ ነው፡፡ ጥንብዝ ብሎ ሰክሯል፡፡ በህልሙ ሲታየው የነበረው የፍርድ ቤት ትዕይንት እና ከነቃ በኋላ ያለው ቅዠት አንድ ሆኖበታል፡፡ “ምን አጥፍቼ ነው እኔ የምከሰሰው” እያለ እንደመነፋረቅ አደረገው፡፡
“ባክህ አቦ ተነስ እና ልበስ! እማማ ትልቋ ሞታለች … አስከሬኗን በመኪና ይዤ መጥቻለሁ… ተነስና ሲስተር ቤት እንሂድ … ተነስ አልኩህ!” አለው ታላቅየው፤ያኛውን በፎደፎደበት በካልቾ ለማለት እየቃጣ፡፡ ታላቅ ወንድምየውም ተኝቶ አለመንቃቱ እንጂ ከታናሽየው ባላነሰ ሁኔታ ሰክሯል፡፡ አይኑ ተጐልጉሎ ወጥቶ ሊወድቅ ይመስላል፡፡
“ተነስ አልኩህ … አንት የተማርክ አህያ! … ደሞ አልጋውን የት አደረስከው … ሰርተህ አትብላና እቃ እያወጣህ ሽጥ”
… ትንሽየው ክንፉ እንደተሰበረ ዝንብ መሬቱ ላይ እያጉተመተመ ይሽከረከራል፡፡ ታላቅየው ብብት እና ብብቱ ስር ሰቅስቆ ገብቶ አነሳው፡፡ ቅድም ከተኛበት ለማንቃት ያረጠበውን ቆሻሻ ፎጣ ጭንቅላቱ እና ማጅራቱ ላይ አለበሰው፡፡ አልብሶት ወደ ደጅ ወጣ፡፡ ትንሽየው በፎጣ የተሸፈነ ጭንቅላቱን ይዞ ይወዛወዛል፡፡ በጥቂቱ መንቃት ጀምሯል፡፡
ያኛው ሲመለስ በነጠላ የተጠቀለለ ድርቅ ብሎ የተገተረ ነገር ተሸክሟል፡፡ በሩ በነጠላ የተሸፈነውን አስከሬን እንዳይነካው ተጠንቅቆ አስገባው፡፡ ባለ ጥጡ ፍራሽ ላይ የሴት አያታቸውን ሬሳ አጋደመው፡፡
ትንፋሹን ሽቅብ ቁልቁል እያለ “ስማ እኔ መኪና ውስጥ አድራለሁ… አንተ ቁጭ ብለህ አስከሬኑን ጠብቅ … ትሰማለህ? ለሲስተር መርዶውን ጠዋት አስነስተን ብንነግራት ይሻላል … በዚህ ሰአት አስከሬን ይዘን ብንሔድ ማዘር ትደነግጣለች፡፡ ጠዋት ቤት ቀስ ብለን ሄደን ለሲስተር እንነግራትና ሲስተር ለማዘር ቀስ ብላ ታርዳት?”
ትንሽየው አሁንም በስርአት አልነቃም፡፡ ተመልሶ መሬት ላይ ቁጭ አለ፡፡ ያኛው እንደገና በካልቾ ሊለው ተንደርድሮ መጣ፡፡ ትንሸየው ለመከላከል ተነስቶ ቆመ፡፡ ታላቁን ማክበር ድንገት ሲያቅተው የታወቀው አይመስልም፡፡ የረጠበውን ፎጣ አንዱ ስርቻ ወርውሮ ሙልጭ አድርጐ ታላቅየውን ሰደበው፡፡ መሐይምነቱን … ከሚሰራው ስራ ያነሰ የሎንቺና ሾፌር መሆኑን … ወዘተ ነገረው፡፡
የታላቅየው ስራ የሎንቺና ሾፌርነት ነው፡፡ አያትየው ከእሱ ጋር ካልኖርኩ ብለው ሰበታ ከሚገኘው የሾፌሩ የወንደላጤ ቤት የገቡት ከወር በፊት ነበር፡፡ ሾፌሩን የልጅ ልጃቸውን ከመምህሩ የበለጠ ይወዱታል፤ እሱም ይወዳቸዋል፡፡
ችግሩ እንክብካቤ እንደሚያስፈልጋቸው እየዘነጋ … በየደረሰበት ከተማ ሲያድር አሮጊቷ እየተጐዱ መሄዳቸውን ልብ አለማለቱ ነው፡፡ ከባድ ሳል ጀመራቸው፤ የኮሶ አረቄ ገዝቶላቸው መፍትሄ እንደሚያገኙ አስቦ ነበር፡፡ ይሄንን አስተሳሰቡን ነው ታናሽየው መሐይም ብሎ የዘለፈው፡፡
ሾፌሩ በታናሹ ከተሰደበ በኋላ ለትንሽ ቅጽበት ፀጥ አለ፡፡ ማስፈራራቱን ግን አልተወም፡፡ “ልብ አድርግ ቁጭ ብለህ አስክሬኑን ጠብቅ፡፡ ተመልሼ ቼክ አደርግሀለሁ … ተኝተህ ባገኝህ … እንደቅድሙ በፎጣ ሳይሆን በድንጋይ ፈጥፍጬህ ከአሮጊቷ ጋር አብራችሁ ትቀበራላችሁ” አለው እና ወጣ፡፡ ወደ ሎንቺናው፤ ገብቶ ለመተኛት፡፡ አሁን ግን ስለተናደደ …እና ግራ ስለተጋባ ቶሎ አይተኛም፡፡ ለአሮጊቷ ሞት ተጠያቂ መሆኑ ውስጥ ውስጡን ሳይሰማው አይቀርም፤ እንቅልፍ አይወስደውም፤ እዛው የመኪናው ኪስ ውስጥ የሸጐጣትን አረቄ አውጥቶ ሲጋት ማደሩ ነው፡፡ ብቻ በሩን ወርውሮ ዘግቶ ሄደ፡፡ የእንጨቷ በር ተገንጥላ ልትወድቅ ነበር፡፡ የጭቃ ቤቱ ግድግዳ ብዙ ጓል አረገፈ፡፡
ትንሽየው እንደዚህ ሰካራም ከመሆኑ በፊት መምህር ነበር፡፡ ከሁለት ሦስት አመታት በፊት፡፡ በአንድ አመት ውስጥ ከሁለት ተማሪዎቹ ጋር የአይን ፍቅር ይዞት … እንደ ጐረምሳ አፈቀርኩ የሚላቸውን እየጠራ በማስፈራራት ፍቅር የሚገለፅ መስሎት የትምህርት ሂደቱን በመበጥበጡ ወደ ሌላ ትምህርት ቤት እንዲቀየር ተደረገ፡፡ ግን መስተካከል አልቻለም፤ ግድግዳ ስር ተለጥፎ ሴቶቹን እየጠበቀ እንደለመደው (ለፍቅር ሲል) ማስፈራራቱ አልተው አለው፡፡ ሴቶቹን የሚያጅብ ወንድ ተማሪን ጥርስ ሲያወልቅ በፖሊስ ተከሰሰ፡፡ ተፈረደበት፡፡ ለስምንት ወራት ታሰረ፡፡ ከእስር ሲፈታ “እስፔሻል ክላስ” ጠጪ ሆነ፡፡
መምህሩ ከመሬቱ ላይ እየተንፏቀቀ ተነስቶ ወደተጋደመው የአያቱ ሬሳ ቀረበ … ነጠላውን ገለጥ አድርጐ አያቸው፡፡
“ሰው ሲሞት የቁመቱ እና የፊቱ ርዝመት ይጨምራል እንዴ?” አለ ለራሱ፡፡ በስካሩ ምክንያት ስለ አያቱ ድንገተኛ ሞት ለማዘን እንኳን አቅም የለውም፡፡ አጠገባቸው ተቀምጦ መጠበቅ ይጀምርና ወለሉ ላይ ተደፍቶ አፈሩ በአፍንጫው ሲገባ ይነቃል፤ ፊቱን በውሃ አጥቦ እንደገና ቁጭ ለማለት ይሞክራል፡፡ በስተመጨረሻ መረረው፡፡ የአሮጊቷን አስከሬን ወደ ግድግዳው አስጠግቶ፣ እንዳይነካቸው ተጠንቅቆ ከጐናቸው ገባና ተኛ፡፡ ገና ጭንቅላቱን ከማሳረፉ ማንኮራፋት ጀመረ፡፡
“የእንግሊዝኛ መምህር እንደመሆንህ አንድ የእንግሊዘኛ ግጥም ጥያቄ እጠይቅሀለሁ” አለው አቃቤ ህጉ፡፡ “ግጥሙን ከጀርባዬ ደብቄ ይዤዋለሁ፤ አንተ የትኛው እጄ ግጥሙን እንደያዘ እና ግጥሙ ምን አይነት እንደሆነ ትነግረናለህ” አለው አቃቤ ህጉ፡፡
“የግጥሙ ቅርፅ ኳርቴት ነው … ገጣሚው ማን እንደሆነ አይታወቅም”
“በትክክል መልሷል፤ ሙሉ ነጥብ ታገኛለህ” አለው አቃቤ ህጉ፤ ሞቅ ካለ ጭብጨባ ጋር
“ግጥሙን በቃሌ ልበልላችሁ”
“ማን ጠየቀህ?!” አለ አቃቤ ህጉ፤ያጨበጨበበት እጁን በመደነቅ ደረቱ ላይ አጣምሮ፡፡ “ሳትጠየቅ መመለስ ፍርድ ቤቱን መዳፈር ነው” ብሎ አስጠነቀቀው፡፡
… “ግን እኮ ሜላት እና ማክዳ አሁን ፍርድ ቤት ውስጥ አሉ፤ አላግባብ መከሰሴን ያውቃሉ፡፡ እኔ የእውቀት ማነስ የለብኝም፡፡ የእንግሊዘኛ ግጥም እንደማውቅ አውቀው እንዲያደንቁኝ እፈልጋለሁ። ስለማያደንቁኝ አይደል የሚንቁኝ? … ስለዚህ ክቡር አቃቤ ህግ፤ ከፍርድ ቤቱ ፈቃድ እያፈነገጥኩ ቢሆንም … በአይን ፍቅር ምክንያት የናቁኝ እነዚህ ሁለት ሴት አህዮች እንዲያደንቁኝ እና እንዲያከብሩኝ ስል ግጥሙን በራሴ ፈቃድ በቃሌ እለዋለሁ”
“As I was going up the stair
I met a man who wasn’t there
He wasn’t there again today-
I wish to God he’d go away”
ግጥሙን በጥሩ አነባበብ በወፍራም ድምፅ ደርድሮ ሲጨርስ፤ እነ ሜላት እና ማክዳ ወደተቀመጡበት ማጅራቱን አዙሮ አይኑ ማተረ። በእነ ሜላት ቦታ ላይ አሮጊቷ አያቱ በነጠላ የተሸፈነ ገፃቸውን ገልጠው በሞት ምክንያት የረዘመ ፊታቸውን አጋልጠው ቁጭ ብለዋል፡፡
በርግጐ ከእንቅልፉ ነቃ፡፡ ወዲያው ቀና አለ፡፡ የአሮጊቷ አስከሬን ከጐኑ ተጋድሟል፡፡ በእንቅልፍ ልቡ አቅፎአቸው እንዳልነበረ እርግጠኛ መሆን አልቻለም፡፡ ዘገነነው፡፡ ጃኬቱን ደርቦ ደጅ አስፋልቱ ዳር ወደቆመችው የወንድሙ ሎንቺና ገሰገሰ፡፡ በሾፌር በር በኩል መወጣጫውን ረግጦ በመስኮት ተመለከተ፡፡
በእንቅልፍ ልቡ መሪው ላይ ላለመደፋት ሲል፤ የአሽከርካሪ ቀበቶውን አስሮ ሾፌሩ ተኝቷል፡፡
በሩን ከፍቶ ታላቅ ወንድሙን ቀሰቀሰው። ሲቀሰቅሰው ባለፈው ምሽት በጀመረው ድፍረት ሳይሆን እንደ ጥንቱ በአክብሮት ነው፡፡ ብዙ ከወዘወዘው በኋላ (በፎጣ መጠብጠብ ሳያስፈልገው) ተነሳ፡፡ ሳይነጋገሩ … ተጋግዘው አሮጊቷን በሎንቺናው የመጨረሻ ወንበር ላይ አጋደሟት። ሬሳው እንዳይንከባለል አሰሩት፡፡ የሁለቱም አይን ተጐልጉሎ ሊወድቅ ምንም አልቀረውም። እህታቸው እና እናታቸው አይናቸውን ሲያዩ ግን በለቅሶ ምክንያት አለመቅላቱን ወዲያው ያውቃሉ፡፡
ሾፌሩ እና መምህሩ ወንድማማቾች፤ በጋቢናው ግራ እና ቀኝ ገቡ፡፡ ሞተሩ ተቀሰቀሰ፡፡ ጋቢናው በሆነ ሽታ ተበክሏል፡፡ አረቄና ምግብ ሲቀላቀሉ የሚፈጠር ጠረን ነው፡፡ አረቄና ምግብ ከውጭ ሆኖ የሚቀላቀሉት ሲመለሱ ወይንም ሲያስመልሱ ብቻ ነው፡፡ ማርሹ ዙሪያ ያለችው ጐድጓዳ ስፍራ ታላቅየው ማታ በጠጣው መጠጥ እና ሀሞት ምልሰት ተሞልታ ተንጣላለች፡፡
አንድ ቃል ሳይለዋወጡ መኪናውን አስነስተው … ለሁለቱም ታላቅ ወደ ሆነችው እህታቸው ቤት በዝምታ ገሰገሱ፡፡  

Published in ልብ-ወለድ
Saturday, 22 February 2014 13:11

የጉዞ ማስታወሻ

ባንግላዲሽ ሲታማ ለኔ ብለህ ስማ---

በባንግላዲሽ ሰዎች ዘንድ ሰውን ትክ ብሎ መመልከት፤ ያውም በቅርበት፤ ነውርነት የለውም። አንዳንዱ ትክ ብሎ ሲመለከትህና “አንተ፤ እገልዬ አይደለህ እንዴ?” ብሎ አቅፎ ሊስምህ ያሰፈሰፈ የሩቅ ዘመድ ሊመስልህ ይችላል፡፡ ትክታው በዝቶብህ፤ ብልጭ ሲልብህ፣ “ምን አባክ አፍጠህ ታየኛለህ? እኔም እንዳንተው ሰው ነኝ፣ አይን አለኝ ጆሮ አለኝ፤…ወይስ ጸጉሬ እንዳንተ የሚያሟልጭ ስላልሆነ ነው?” ብለህ ግብግብ ልትገጥም ሁሉ ትችላለህ። በዚያ ላይ የባንግላዲሽ ሰው ቀጭንም አጭርም ስለሆነ፣ የመጣው ይምጣ ብለህ ትግል ብትያያዝ እንኳ ቢያንስ ከታች እንደማትውል እርግጠኛ ነህ፡፡ በዚህም የተነሳ ለፀብ ልትገፋፋ ትችላለህ፡፡
አብራኝ የነበረችው የጉዞና የስራ ባልደረባዬ ወ/ሮ ህይወት እምሻው፤ ትክታቸው ምርር ብሏት “እኔ የምልህ፤ ተስፍሽ እኔን ብቻ ነው አንተንም ነው እንደዚህ ትክ ብለው የሚያዩት? ቀለሜን አስለቀቁት’ኮ” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ “አንቺ ጋ የመጡት እኔን አጠውልገው ነው” ብዬ ላስቃት ሞከርኩ፣ ግን አልተሳካልኝም፡፡ ምክንያቱም፤ ተበሳጭታለች!
ሌላ ደግሞ፤ በባንግላዲሽ ሰዎች ዘንድ አበሻ “ገመና” የሚለው አሊያም ፈረንጆች “ፕራይቬሲ” የሚሉት ነገር የሚታሰብ አይደለም፡፡ ወደ ባንግላዲሽ ዋና ከተማ ወደ ዳካ ለመጓዝ ዱባይ አውሮፕላን ጣቢያ ላይ የተቀበለኝ ትክታቸው በምን እንደሸኘኝ ልንገራችሁማ፡፡ የሰነበትኩበትን ሆቴል በጠዋት ለቅቄ እቃዬን እንግዳ መቀበያ ክፍል አኑሬ ስለነበር፣ ማምሻዬ ላይ ለጉዞ እንዲመቸኝ ብዬ የሻንጣዬን እቃዎች ወዲያ ወዲህ ሳደርግ፣ የሆቴሉ ባልደረባ ወደኔ መጣ፡፡ መቼም እንግሊዝኛ የለም፤ በምልክት “ልርዳህ?” አለኝ፡፡ ፈቃድ መጠየቁ አልነበረም፡፡ ሰው ተቸግሮ እያዩ ፈቃድ መጠየቅ ምን ያደርጋል? የሚል ይመስላል - “እንግዳ ተቀባይ ወጣቱ” ባንግላዲሽያዊ፡፡
“ታንክ ዩ” አልኩትና ሽከፋዬን ቀጠልኩ፡፡ ያ ሰው ታዲያ አጠገቤ ቆሞ የእቃዬን ዝርዝር ይመለከት ጀመር፡፡ “ሰሞኑን ብርድልብስ ጠፍቶባቸው ይሆን እንዴ?” ብዬ ለራሴ ቀለድኩ፤ በሆዴ፡፡ ይግረምህ ብሎ በጣም ተጠግቶ መመልከት ጀመረ - ክሎዝ አፕ ፎቶ እንደሚያነሳ የሰርግ ፎቶ አንሺ፡፡ ቋንቋዬን ባያውቅም፤ ቀልደኛ ሰው ከራሱም ጋር ይቀልዳልና፤ ልክ ልኩን ልንገረው ብዬ “ምን ይገትርሃል?” አልኩት፤ በአማርኛ፡፡ “ብቆም ምን አለበት? እቃህን በአይኔ ነው እንጂ በእጄ አልነካሁብህ!” ያለኝ መሰለኝ፤ በባንግላዲሽኛ፡፡
የአገሬ ሰው ስለ ገመና፣ ስለ ሰው ምስጢር፣ የሰውን ነገር ያለፈቃድ ስላለማየት ያለውን የ “መመሪያ” ጥራዝ በአይነ ህሊናዬ ለአፍታ አነበብኩ። ባንግላዲሻውያን በሌላኛው ጠርዝ ላይ ነው ያሉት። አበሻም በራሱ መንገድ እንደሚያበዛው ደሞ ልንገራችሁ፡፡ አንቱ የተባለ፤ እኔ ነኝ ያለ ታዋቂ ሰው መጥቶ አጠገባችን ቆመ እንበል፡፡ ስንታችን እንሆን “ጤና ይስጥልኝ፤ እገሌ ነህ አይደል? ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ በጣም እንደማደንቅህ እና እንደማከብርህ ልነግርህ እወዳለሁ” ብለን ለመጨበጥ እጃችንን የምንዘረጋው? ያን ሰው በቆረጣ ስናይ ቆይተን (ሰውየው) ከዚያ ቦታውን ለቆ መንቀሳቀስ ሲጀምር ወይም ርቆ ከሄደ በኋላ “እንትና ነው’ኮ፤ ሾፍከው?” ነው የምንባባለው፡፡ እንኳን ተራን ሰው ዝነኞቻችንን እንኳ ትክ ብለን የማናይ ሰዎች ነን ለማለት ያህል ነው፡፡
ለማንኛውም ሁለቱም ጫፍ ጤናማ አልመሰሉኝም፡፡ ስለራሳችን እናውራ ካልን “ትህትናችን” ከልክ ያልፋል፡፡ ፈታ ፈታ ብለን እንግዶችን እንዲሁም ታዋቂ ሰዎችን ማነጋገር እንልመድ፤ አይመስላችሁም? ወደን በተቀላቀልነው እድር ውስጥ የማናውቀው አባል ከጎናችን ለሰዓት ተቀምጦ ሲነሳ የማነጋግር አለን አይደል? የንግድ ማህበር አባል ሆነንም የማናውቀውን ሰው “እገሌ እባላለሁ፣ የምኖረው … ወዘተ” መች እንላለን? ወይም… እንበል በቃ!
ባንግላዴሻውያን ምግባቸው ቅመም በቅመም ነው፡፡ በተለይ በተለይ በየምግቦቻቸው ውስጥ ሁሉ የምትገባ አንድ ቅመም አለች፡፡ ራት ስንበላ “ይቺን ቅመም የማውቃት መሰለኝ” አልኩ ለወ/ሮ ህይወት፡፡ ከማወቅም አልፎ ልጅ ሳለሁ ተክዬ ወይም ዘርቼ፣ ዘሯን አበርክቼ የማውቅ ሁሉ መስሎ ተሰማኝ፡፡ ትንሽ ቆይቼ ምንነቷና ስሟ ትዝ አለኝ፡፡ ማን መሰለቻችሁ? ድንብላል! ለህይወት ስነግራት “ልክ ነህ ልጄ፤ ድንብላል---አዎ ድንብላል” አለች፤ የዘመዷን ስም የረሳች ያህል እንደተፀፀተች በሚገልጽ ድምፀት ጭንቅላቷን እየናጠች፡፡ “እማ አገርም’ኮ…” ብላ ቀጠለችበት፡፡
የራሴን ትዝብት ላውራችሁና … ድሮ፣ ድሮ ድንብላል ምግባችን ውስጥ ይዘወተር ነበር፡፡ አሁን አሁን ቀረ ልበል? ግን ለምን ይሆን? ትንሽ ስቆይ ጥሌ ሁሉ ከዘፈኖቹ በአንዱ ውስጥ እንዳነሳት አስታወስኩ። “ጥሩ መቼ ጠፋ ከቅመም ድንብላል፤ ከሴት አንችን አየሁ አይንሽ ያባብላል” (መሰለኝ) ብሎላታል፡፡ ከቅመም ምርጡ ድንብላል ነው። ከውበት ደግሞ የማይታለፈው አይን ነው ማለቱ መሰለኝ፤ የዘፈኑ ደራሲ፡፡ እስቲ ሰሞኑን ወደ ቅመም ተራ ወጥቼ የድንብላል ዋጋ ስንት እንደ ደረሰ እጠይቃለሁ፡፡
በዳካ ከተማ ብሎም በሌሎች ባየኋቸው ከተሞች ውስጥ ፌስታል የለም፡፡ እቃ የሚገዛ ሰው የሚያምር የወረቀት ፖስታ ይሰጠዋል፡፡ ፖስታው በጋዜጣ የተሰራ ሊሆን ይችላል፤ አሊያም ከክርታስ ብጤ፡፡ ከትላልቅ የገበያ አዳራሾች ጀምሮ እስከ ዳካ የአየር ጣቢያ የቀረጥ ነጻ ሱቆች ድረስ የሚሰራባቸው ባለማንጠልጠያ ወረቀቶች ናቸው፡፡ ከተማዋ የራስዋ ቆሻሻ አላት፤ ፌስታል ግን የትም አይታይም፡፡ አገሪቱ በአቋም ደረጃ ፌስታልን እንዳገደች መጠየቅ አላስፈለገኝም፡፡ ያ ሁሉ ህዝብ የሚተራመስባት አገር ያለፌስታል መኖር ከቻለች አዲስ አበባ (ቆጨኝ)… እኛ’ኮ እንደ ወፍራም ሸክላ ምጣድ ብዙ የኑሮ እሳት ከለበለበን በኋላ፣ ቆይተን ነው የምንሰማው፡፡
የባንግላዲሻውያን የመኪና አነዳድ ያስጨንቃል። ስርዓት ብሎ ነገር የላቸውም፡፡ “ማሪኝ አዲስ አበባ” ያሰኛል፡፡ አሽከርካሪዎች ከግራ ወደ ቀኝ ጫፍ እየተሽሎከሎኩ ሲበሩ ማየት የየጎዳናው ትዕይንት ነው፡፤ የሚያጣድፍ ጉዳይ ያለውም የሌለውም ይከንፋል፡፡ ሽል ሽል፤ ሽው ሽው፤ ላጥ ላጥ፤ ዘው ዘው- እንደዚያ ነው አነዳዳቸው፡፡ ቀዥቃዣ የተባለ የአዲስ አበባ ታክሲ ሾፌር ዳካ ደርሶ ቢመለስ ወይ አብዶ አሊያም ሰክኖ ይለይለታል ብዬ አስባለሁ። ባለሁለት እግር፣ ባለሶስት እግር ብስክሌቶች፣ ሞተር ብስክሌቶች፤ ባጃጆች፤ በእንስሳ የሚጎተቱ ጋሪዎች፣ እጅግ ዘመናዊ የሚባሉ አውቶሞቢሎችና ከባድ መኪናዎች ሁሉም ተመሳሳይ አነዳድ ነው ያላቸው - መሬት ይዘው ይበራሉ፡፡ በዚያ ላይ ጥሩንባቸው ለጉድ ነው፡፤ መሪ የጨበጠ አሽከርካሪ (ሾፌር) በሙሉ ይሄ ነው ሊባል በማይችል ምክንያት ጥሩንባ ሲያንጣርር ነው የሚውለው። ወደ አዲስ አበባ ከተመለስኩ በኋላ መንገዶችን ሳዳምጥ በፀጥታ የተሞሉ ሆነው ነው ያገኘኋቸው። ከመሄዴ በፊት አዲስ አበባን በጥሩምባ ብዛት ከዓለም የሚስተካከላት የለም ብዬ በጣም አዝን ነበር፡፡ ብራቮ የአገሬ አሽከርካሪዎች! እባካችሁን ከዚህ የበለጠም እንሁን፡፡ በተለይ ትራፊክ መብራት ገና ከመልቀቁ አምስት ሰከንድ እንኳን ሳይታገሱ ጡሩንባቸውን የሚለቁ አሽከርካሪዎች ከትዕግስት ጋር እንዲለማመዱ እመክራቸዋለሁ፡፡
ባይገርማችሁም በዳካ ከተማ ውስጥ የእግረኛ ማቋረጫ (ዜብራ መንገድ) አላየሁም፡፡ እግረኛው ቁርጡን አውቆ መንገድ የሚያቋርጠው እየሮጠ ነው፡፡ “እግሬ አውጪኝ”፤ ትክክለኛ አገሩ ዳካ መሆን አለበት፡፡ ሁሉም ያዋጣኛል ባለው መንገድ ነው የሚያቋርጠው፡፡ እንደ አዲስ አበባ እግረኛ በሁለት እግሩ (ጫማ) መንገድ እየለካ የሚሄድ የለም፡፡ እንቀራፈፋለሁ ካለ ከከባድ መኪና ቢያመልጥ ከሞተር ብስክሌት አያመልጥማ፡፡ “ለእግረኛ ቅድሚያ ሲዳላ ነው” ብያለሁ፡፡ አስር ሚሊዮን ህዝብ ችርችም ብሎ ባለበት ከተማ ውስጥ “እግረኞች በዜብራ መንገድ ተሻገሩ” ቢባሉ አሊያም “አሽከርካሪዎች ለእግረኛ ቅድሚያ ስጡ” ቢባሉ ማንም የትም መንቀሳቀስ አይችልም ነበር። በነገራችን ላይ አሽከርካሪምች የግራ፣ የመሃል ወይም የቀኝ መስመራቸውን (ሌናቸውን) ጠብቀው እንደማይነዱት ሁሉ የከተማው ሰውም ለሰልፍ ተራ ደንታ የለውም፡፡ ሰዎች ሰልፍ ይዘው እያለ አንዱ ያለ ምንም ቅሬታ ከመሃል ጥልቅ ሊል ይችላል፡፡ “አሃ” ያልኩት እዚህ ጋ ነው፡፡ አሃ! ኋላ ቀርነትና ስርዓት አልባነት አይነጣጠሉምና!
ዳካ ውስጥ ብዙ ሰዎች በተሽከርካሪ አደጋ ይሞታሉ፡፡ ከዳካ 40ኪሎ ሜትር ወጣ ብላ ወደምትገኝ ከተማ ለስራ ጉዳይ ሄደን ነበር፡፡ የጤና ጣቢያ ኃላፊው፤ ልጆችን ለህመም የሚዳርጉና ገዳይ የሆኑ በሽታዎችን ሁለት ጠርቶ ሶስተኛውን “የመኪና አደጋ ነው” አለን፡፡ አንደኛ ምክንያት ያለመሆኑም ይገርማል፡፡ አናሳዝንም ግን? እነማን መሰልናችሁ? እኛ በስልጣኔና በሀብት ወደ ኋላ የቀረን፣ ለህይወታችን ዋጋ የማንሰጥ፣ ለንብረታችን የማንጠነቀቅ፣ዝም ብለን በራሳችን ጥፋት የምናልቅ ህዝቦች!
ወጣ ካልንበት ስንመለስ የመኪናችን ሾፌር ጤነኛ አልመስላችሁ አለን፤ ከፊት ለፊት ከሚመጣ መኪና ጋር ለመጋጨት እናም ነፍሱን ለማጥፋት የቆረጠ ይመስላል፡፡ ቀስ በል እንዳንለው በምን አፍ። በዚያ ላይ ብስክሌቱ፣ በበሬ የሚሳበው ተሽከርካሪ፣ አውቶቡሱ ሁሉ የሚተራመሰው በጠባብ መንገድ ላይ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም አዲስ አበባን ጎብኝቶ የመጣ አንድ የስራ ባልደረባችን ባንግላዲሻዊ “ባንግላዲሽ እንደ ኢትዮጵያ አልታደለችም፤ የቀለበት መንገድ የላትም፡፡ ለምን መሰለህ? ከተማዋ በውሃ የተከበበች ናት፡፡ አራት ጊዜ የሚያቋርጣት ወንዝ አለ፡፡ ያንን ሁሉ አርቆ መሰረት አውጥቶ መንገድ መስራት ያስቸግራል” አለኝ፡፡ ለቀለበት መንገድም መታደል ያስፈልጋልና!
የባንግላዲሽ ዋና ከተማ በዛፎች ብዛት የሚስተካከላት ያለ አይመስለኝም - የሰው ግምት ባየው ወይ በሰማው ልክ አይደል እንግዲህ፡፡ ከአውሮፕላን ጣቢያ የተቀበለን ሾፌር እንዲህ ብሎኝ ነበር፤ በተዘበራረቀ እንግሊዝኛ “ዳካ ግሪን ኢዝ”፤ (ዳካ አረንጓዴ ናት ማለቱ ነው፡፡) እውነቱን ነው። ህንፃ ያላረፈባቸው ቦታዎች ሁሉ በትላልቅ ዛፎች ተሸፍነዋል፡፡ የግለሰብ ቤት ግቢዎች፣ የመንገድ ጠርዞች እና ተንጠልጣይ ሳጥኖች ሁሉ ዛፎች፣ ቢያንስ ትናንሽ ተክሎች ይታዩባቸዋል፤ ስደነቅ አደርኩና በነጋታው እግሬን ላፍታታ ማልጄ ወደ ደጅ ወጣ ስል መንገዱን ጦጣዎች ሲንሸራሸሩበት ተመለከትኩ፡፡ ዛፍ ተመችቷቸው ከቅርንጫፍ ቅርንጫፍ ይዘላሉ፡፡ አልፎ ተርፎ ፎቅ ላይ መወጣጫ እየፈለጉ ይጓጓዛሉ። ከመንገደኛው የሚሰጣቸውን ጉርሻም ይቀበላሉ፡፡
ያየሁት ነገር እጅግ ስለደነቀኝ አንድ የአገሩን ተወላጅ ስለ ትዝብቴ ነገርኩት፡፡ ይህ ሰው የአንድ አለም አቀፍ ድርጅት ባልደረባ ነው፡፡ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችግር የለበትም፡፡ እና፤ “ልክ ነህ፤ ጥሩ ታዝበሃል፡፡ ከተማችን ብዙ ዛፎች አሏት” አለ ኮራ ብሎ፡፡ ቀጠለበት፤ “እንዴት መሰለህ? ከዚህ በፊት ብዙ ጊዜ ንፋስ ይመላለስብን ነበር፡፡ በየጊዜው የሚያላጋ አደጋ ብዙ ሰዎችን ይጨርስብንም ነበር። በኋላ መንግስት መከረበትና ንፋስ-አግድ ዘዴ አድርጎ የዛፍ ተከላን አወጀ፡፡ እንደታሰበው የአደጋው መጠን በእጅጉ ቀነሰ፡፡ ነገርየው የተጀመረው በቅርቡ ቢሆንም አሁን ዛፍ መትከል የዳካ ነዋሪዎች ባህል ነው” አለኝ፡፡
ከዛፎች መልማት በኋላ የሆነውን ነገር ማሰብ አላቀተኝም፡፡ አጅሬ ንፋስ እንደለመደው እየከነፈ ሲመጣ፣ ዛፎች በቅርንጫፎቻቸው ሰነጣጥቀው ሃይሉን ያዳክሙታል፡፡ ከዚያ፤ ካሻው አውሎ ነፋስ ሊሆን እያፏጨ የመጣው ነፋስ፣ የት እንደ ደረሰ ሳይታወቅ ብትንትኑ ይወጣል፡፡
የሳምንት ቆይታዬን አጠናቅቄ ስመለስ ከቡድኔ አባላት ጋር የባንግላዲሽን ዋና ከተማ ዳካን፤ ከዳር እስከዳር የመጎብኘት እድል ገጠመኝ፡፡ አስጎብኚያችን “ያ የምታዩት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ነው፡፡ ያኛው ደሞ የፓርላማ ጽ/ቤት ግቢ ነው። ከዚያ ህንጻ ጎን ያለው ትልቁ የዳካ ዩኒቨርሲቲ ነው …” ይለናል፡፡ አቤት የዛፍ ብዛት! መሀል ከተማ ውስጥ ያለውን የወፎች ዝማሬ ድምቀት ለማመን ያስቸግራል፡፡ በዚያ ላይ ዛፎቻቸው በአይነት የተለያዩ ናቸው፡፡ በፎቶግራፍም ሆነ በቴሌቪዥን አይቼ የማላውቃቸው ብዙ ዛፎች አጋጥመውኛል፡፡ የካካዋ ዛፎች በብዛት አሉ፡፡
ወደ መናፈሻ እና መተናፈሻ (ክፍት) ቦታዎች ስንመጣ፣ ዳካ ለወጣትና አዛውንቶቿ ሙት መሆኗን ተረዳሁ፡፡ ለእግር ጉዞ የሚመቹ፣ ግራና ቀኛቸው በትላልቅ ዛፎች የተከለሉ ብዙ መንገዶች እና በርካታ ጊዜ ማሳለፊያ መናፈሻዎች አሏት፡፡ ይታያችሁ! ያውም’ኮ አስር ሚሊዮን ህዝቦች የሚኖሩባት ከተማ ናት፡፡ ብዙ አስቀያሚ ቦታዎች እንዳሏቸውም ሰምቻለሁ፤ አይቻለሁም፡፡ ዛፍ አልባ ግን አይደሉም።
ከዳካ ሳልወጣ አዲስ አበባችንን ቃኘት አደረግሁ - በምናቤ፡፡ አዲስ አበባም’ኮ ህዝቡም የከተማ አስተዳደሩም ተረባርቦ ብዙ ዛፎችን ተክሏል፡፡ (ጋሽ አበራ ሞላ የምስጋና ድርሻውን የሚከለክለው የለም ብዬ ነው፡፡) የመንገድ መሃሎች፤ ለምሳሌ ቸርችል ጎዳና፤ አራት ኪሎ ቀደም ሲል መች ዛፍ ነበራቸው? እያልኩ ተደሰትኩ፡፡ እርግጥ ነው ብዙ አዳዲስ መንገዶች ለዛፍ መትከያ የተተወላቸው ቦታ ጥበቱ ይሰቀጥጣል፡፡ ለወደፊቱ ቀጫጭን እንጂ ወፋፍራም ዛፎች በዚያ ቦታ ላይ የመቆየት እድል አይኖራቸውም፡፡ በተረፈ ግን አዲስ አበባችን ከአንድ ሶስት አመት በኋላ በዛፎች የተዋቡ መንገዶች ይኖሯታል፡፡ አዲስ አበባ የምትተነፍሰውን ኦክስጂን ከየት ለማግኘት አስባ ይሆን ዛፎቿን የጨረሰችው? ብዬ ተገረምኩ፡፡
በኦክስጂን ራሳችንን ስለመቻልም እናስብ እንጂ! መናፈሻማ የማይታሰብ ነገር እየሆነ ነው፡፡ ፒያሳ በሉ አራት ኪሎ የምሳ እቃ ይዞ ከቤቱ የወጣ ሰው፣ ለአንድ አስር ደቂቃ ቁጭ ብሎ የሚነሳበት ጥላ ቦታ የት ነው ያለው? ጊዜው ቆይቷል፤ በብዕር ስሙ “ዳንዴው ሰርቤሎ” የተባለ ፀሃፊ፤በሬዲዮ የተናገረው ይሁን ያነበበው  ነገር መቼም ከጆሮዬ አይወጣም። የመልእክቱ ጭብጥ እነሆ፤ “ጊዮርጊስ አካባቢ፣ ከማዘጋጃ ቤቱ በስተግራ፣ ከአያሌው ሙዚቃ ቤት ፊት ለፊት ባለው ክፍት ቦታ ላይ ህንጻ ተሰርቶ ሳላይ ብሞት ደስ ይለኛል” ነበር ያለው፡፡ ዳንዴው ስለ መናፈሻና መተናፈሻ ያለው ግንዛቤ በወቅቱ አስደስቶኛል፡፡ በዚያ ባለው ቦታ ላይ የህንጻ ስራው ግን ተጀምሯል፡፡ ይህ ሰው እንደዚያ ያለው ከቦታው  ጋር የተለየ ፍቅር ኖሮት ሳይሆን አንድ መናፈሻ-መተናፈሻ ቦታ ፒያሳ ውስጥ ያስፈልጋል ለማለት ፈልጎ እንደሆነ እረዳለሁ፡፡
ከጥቂት አመታት በኋላ ሀብታም ስንሆን፤የተወሰኑ የአዲስ አበባ ህንፃዎች ተገንድሰው መሬቱም ተጠርጎ መናፈሻ እንደሚሰራ እገምታለሁ። “ጠብ ሲል፤ ስደፍን፣ ጠብ ሲል፤ ስደፍን” የሚለው የቆርቆሮ ማስታወቂያ አሁን የት ደረሰ? ጎበዝ፤ በተለይ ወንዶች፤ ለጊዜው ባሉን ክፍት ቦታዎች ሁሉ አትክልትና ዛፎችን እንትከል እባካችሁ፡፡ ሴቶችማ በየጣሳው፣ በየባልዲ ቁራጩ፣ በየቀለም ቆርቆሮው፣ በየመድፍ ጥይት ቀለኹ ውስጥ ሳይቀር አትክልት እየተከሉ ቤታችንን እያስጌጡ ነው፡፡
ባንግላዲሽ የእንግሊዝኛ ተናጋሪ እጥረት አለ። የእንግሊዝ ቅኝ ግዛት እንደነበረች፣ ወዲህም የህንድ ጎረቤት መሆንዋን በማሰብ ብዙ እንግሊዝኛ ተናጋሪ አገኛለሁ የሚል ግምት ነበረኝ፡፡ አልሆነም፡፡ ከሆቴል አስተናጋጅ እስከ ባለሱቅ ድረስ ያለ እንግሊዝኛ ነው የሚኖሩት፡፡ የሆቴል እንግዳ ተቀባይ እጅግ የተወሰኑ ቃላትን ብቻ ያውቃል፡፡ የባንግላዲሽ በረከት የሆነውን ፐርል የሸጠልኝ ሰውዬም “ሰር ፎር ዩ፤ አዘር ኖ” (ላንተ ብዬ ነው፤ ለሌሎች እንደዚህ ባለ ዋጋ አልሸጥም) ከማለቱ ውጭ ሌላ የተናገረው እንግሊዝኛ ትዝ አይለኝም፡፡ ነጋዴ ሁሉ አንድ ነው አትሉም። አንድ ቀን ያወቀኝን ሰውዬ የነፍስ ደንበኛ አድርጎ ለመደለል መሞከሩ አሳቀኝ፡፡ የመርኬ ነጋዴ ምን ያህል እንዳሰለጠነኝ በምን አፍ ልንገረው። ኢትዮጵያውያን ከዳር ዳር እንግሊዝኛ ተናጋሪ አለባቸው፡፡ ቋንቋውን ቅርጥፍ አድርገው በልተው ቅልጥፍ አድርገው የሚናገሩ ሰዎችን ብዛት አሰብኩ። አየር መንገድ፣ ባንክ፣ ወዘተ፡፡ በሀሳቤ መሀል ሌላ ሀሳብ ሰረቀኝ፡፡ እንደ ባንግላዲሾች እንግሊዝኛን ገሸሽ ብናደርገውስ? እንግሊዝኛ የጣለው የአገሬ ወጣት በአይኔ ላይ ሽው ሽው አለ፡፡
“ኖ ፋይት?” አለኝ፤ኢትዮጵያ ውስጥ ማለቱ ነው።
  “ኖ! እንኳን አገሪቱ በሬም እርስ በርስ መዋጋት ትቷል” አልኩት፡፡
ዳካ የመጨረሻ ደሀ ሰፈር፣ የመጨረሻ አሪፍ ሰፈር አላት፡፡ የድሆቹን ገባ ብዬ አላየሁም፤ የሀብታሞቹን ግን ለማየት ችያለሁ፡፡ በሰባት ሺህ ዶላር የተከራየ ቤት ውስጥ ጥሩ ፒዛ በልቻለሁ፡፡   



Published in ጥበብ

        ከተመሰረተ ስልሳ አምስት አመቱን ያስቆጠረው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ አለምአቀፋዊ ተቋምነቱ እና የብዙዎችን ይሁንታ ያገኘበት ሀላፊነቱ በተግባር በሚያከናውነው ስራ አንፃር ሲመዘን ጥያቄ ላይ የወደቀ ድርጅት ነው፡፡ አሁን በሀላፊነት ላይ ያሉት የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ፀሀፊ ባን ኪ ሙን የመንግስታቱን ድርጅት የመለወጥ ሀሳብ በተደጋጋሚ ያነሳሉ፡፡ ነገር ግን፣ ድርጅቱን በዋና ፀሀፊነት ካገለገሉ ስምንት ሰዎች ውስጥ አንዱ ብቻ ናቸው ስለ ለውጥ ምንም ተናግረው የማያውቁት፡፡ የተወሰኑ ለውጦች በተለያዩ ጊዜዎች የተደረጉ ቢሆንም፣ በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ግን ምንም አይነት ለውጥ አለመደረጉ ጥያቄዎቹ ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲበረቱ አድርጓል፡፡
በድርጅቱ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች የአባል አገሮቹን ያህል የበዛ እና የተወሳሰበ ቢሆንም፣ በማሻሻያዎቹ ላይ ጥናት ያደረገው ዛክ ቱከር፣ ጥያቄዎቹን በሶስት ዋና ዋና ምድቦች ይከፍላቸዋል። አንደኛው ጥያቄ፡- በመንግስታቱ ድርጅት ውስጥ እንደ ባህል የተያዘውና እንደ አሰራር እየተከተለ ያለው መንገድ፣ ውሁዳን ሊሂቃንን ያካተተው የአባል አገሮች ቡድን የመንግስታቱን ድርጅትም ሆነ የአለም ፖለቲካ አድራጊ እና ፈጣሪ የሚያደርጋቸው ነው፡፡ ሁለተኛው ጥያቄ የሚያተኩረው ደግሞ፡- በመንግስታቱ ድርጅት እንደ አንድ ግብ የተቆጠረው ግሎባላይዜሽን በአባል አገሮች ሉኣላዊነት ላይ እየጋረጠ ያለው ስጋት ላይ ነው፡፡ ድርጅቱ ግጭቶችን በመከላከልም ሆነ ሰብአዊ ቀውስ በሚፈጠርበት ጊዜ ሰብአዊ አገልግሎቶችን በብቃት አይወጣም የሚለው ሶስተኛው ጥያቄ ነው፡፡
በለውጡ ላይ የድርጅቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ምክር ቤት ትልቅ ቦታ ሊሰጠው ይገባል። በድርጅቱ ቻርተር መሰረት የምክር ቤቱ ሚና ወደ ጥናት እና አማካሪነት ያተኮረ ነው፡፡ ነገር ግን፤ በሚሰራበት የምርምር፣ የባህል፣ የትምህርት፣ የጤና እና ተያያዥ ዘርፎች ላይ ልክ እንደ ፀጥታው ምክር ቤት  በድርጅቱ ስም ውሳኔ ማስተላለፍ የሚችልበት አቅም ሊሰጠውም ይገባል፡፡ ይህ መደረጉ ደግሞ በድርጅቱ ውሳኔ ላይ የብዙሃን ድምፅ እንዲካተት እና በተለይ በአሁኑ ወቅት ክፍተት ያለበት ከሰብአዊ ድጋፎች ጋር የተያያዙ ስራዎች ምላሽ እንዲያገኙ ያስችላል ይላል ዛክ፡፡
የመንግስታቱ ድርጅት ላይ ለውጥ ሲነሳ፣ የብዙዎችን ትኩረት የሚስበው የፀጥታው ምክር ቤት ነው፡፡ ምክር ቤቱ፤ አራቱን የሁለተኛው የአለም ጦርነት አሸናፊዎች ማለትም አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ሩሲያ እና ቻይና በቋሚ አባልነት  እና በየሁለት አመቱ የሚቀያየሩ አስር ተለዋጭ  አባላትን ይይዛል፡፡ ይህ ምክር ቤት ከሰላም እና ከደህንነት ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ከፍተኛው የድርጅቱ ክንፍ በመሆኑ ማዕቀቦችን ይጥላል፣ የሀይል እርምጃዎችን ያፀድቃል ወይንም ይሽራል፡፡ ውሳኔዎችን ተግባራዊ ለማድረግ የዘጠኝ አባላት ድምፅ ሲያስፈልግ የቋሚ አባላቱ ሙሉ የስምምነት ድምፅ ግን የግድ ያስፈልጋል፡፡
የመንግስታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ላይ በሚነሱ ጥያቄዎች እና ለማሻሻያ ይረዳሉ በሚል በተጠራ የከፍተኛ ባለሙያዎች ፓናል ሪፖርቱን ለድርጅቱ አቅርቧል፡፡ በፓናሉ ላይ የመንግስታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክርቤት የተሰጠውን ሚና መወጣት እንዳቃተው ሪፖርቱ ያሳያል፡፡ በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት ከሞላ ጎደል ሽባ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ከቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃት በኋላ የመነቃቃት አዝማሚያ ቢታይም፣ ከተወሰኑ ውጤታማ ስራዎች በስተቀር አንድን አሳሳቢ ጉዳይ ከመከሰቱ በፊት ለመከላከል ወይም ለተፈጠረ ቀውስ መፍትሄ ከማምጣት ይልቅ የሀይል መጠላለፍ እና መቆላለፉ በመጉላቱ፣ ቋሚ የምክር ቤቱ አባሎች ጥቅም ማስጠበቂያ ሆኗል፡፡ በተለያዩ ጊዜዎች ምክር ቤቱን ለማሻሻል የተደረጉ ሙከራዎች በተለይ የምክር ቤቱ አባልነት ላይ ይደረጉ በሚባሉ ማሻሻያዎች ስምምነት ላይ ባለመደረሱ ውድቅ ሲሆኑ ተስተውለዋል፡፡
በፓናሉ ላይ የምክርቤቱን አባላት ቁጥር ከአስራ አምስት ወደ ሀያ አራት በማሳደግ ሁለት ሞዴሎች ለውይይት ቀርበው ነበር፡፡ አንዱ ሞዴል፡- ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት የሌላቸው ስድስት አዲስ የቋሚ አባላትን ማካተት ሲሆን፣ ሁለተኛው ሞዴል ደግሞ አዲስ የቋሚ አባላትም ሳይኖሩ በየአራት አመቱ የሚለዋወጥ መቀመጫ ይኑር የሚሉ ናቸው፡፡
የፀጥታው ምክር ቤትን ጉዳይ አስመልክቶ የተሰጡ ብዙ አስተያየቶች አሰራሩ መሻሻል እንዳለበት ይጠቁማሉ፡፡ አምስቱ አገሮች በሞኖፖል ጠቅልለው የያዙት ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት በራሱ ከመሰረታዊዎቹ የህግ መርሆዎች ጋር ይጋጫል፡፡ አገሮቹ ውሳኔዎች እንዲያልፉ ወይም እንዲወድቁ ድምፅ የሚሰጡት ከሰብአዊ መብቶች ወይም ከአለም አቀፍ ህግ በመነሳት ሳይሆን፣ ከራሳቸው መንግስት ጥቅም እና ፍላጎት አንፃር ነው። የፀጥታው ምክር ቤት የተቋቋመው አለም አቀፍ ሰላም እና ደህንነትለ ለማስከበር ቢሆንም እያገለገለ ያለው ግን ለየአገሮቹ የኢኮኖሚ ጥቅም እና የጡንቻ ብቃት መለኪያነት ነው፡፡ ምእራባውያኑ በአለም ላይ ዲሞክራሲን የማስፈን እውነተኛ ፍላጎት ካላቸው ሥራው መጀመር ያለበት በመንግስታቱ ድርጅት፣ በተለይም በፀጥታው ምክር ቤት ነው፡፡ ድምፅን በድምፅ የመሻር መብቱ የተሰጠው ፍትሀዊ ባልሆነ መንገድ በመሆኑ ሰላም ማምጣት አልተቻለም፡፡ ይህ አሰራር፣ ክፍፍል እና ብዙ ተቃርኖ ያላቸው ቡድኖች እንዲፈጠሩ እድል ሰጥቷል፡፡ ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት በመንግስታቱ ድርጅት ውስጥ ያለ የዲሞክራሲ መርሆችን የሚሸረሽር አሰራር ነው፡፡
በአለም ላይ ያሉ አገሮችና ህዝቦች እጣፈንታ በአምስት አገሮች ፍላጐት እንዲወሰን በመፈቀዱ ምክንያት አለማችን ይሆናሉ ተብለው የማይገመቱ እልቂቶችንና አሳዛኝ ክስተቶችን እንድታስተናግድ ምክንያት ሆኗል፡፡ የሩዋንዳው እልቂት፣ የዳርፉር እና የሶሪያ ሰብአዊ ቀውሶች እንደ ምሳሌ ይጠቀሳሉ። የመንግስታቱ ድርጅት ሩዋንዳ ውስጥ የተከሰተውን የዘር ማጥፋት እልቂት ቀድሞ መከላከል ያልቻለው ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ባላቸው አሜሪካን እና ፈረንሳይ ውሳኔ ነው፡፡ ሁለቱ አገሮች ከየጥቅሞቻቸው በመነሳት፡- አሜሪካ ከገንዘብ ጋር በተያያዘ፣ ፈረንሳይ ደግሞ አጋሮቿን ላለማጣት በሚል የግል ስሌት ውስጥ በመግባታቸው  ነው … ብዙሀን በአደባባይ እንደ በግ የታረዱት። የሲሪላንካው አማፂ ቡድን “ታሚል ታይገርስ” ላይ በመንግስት በኩል ይደርሱ የነበሩ ኢ-ሰብአዊ እርምጃዎችን ለመታደግ በሚል መንግስት ላይ ሊጣል የነበረ ማእቀብ ውድቅ የተደረገው በቻይና ሲሆን መነሻውም ቻይና ከሲሪላንካ መንግስት ጋር ያላትን ወዳጅነት ላለማሻከር ሲባል ነበር፡፡ ሶስተኛ አመቱን የያዘውና  በመንግስታቱ ድርጅት የዘመኑ ከፍተኛ ሰብአዊ ቀውስ የታየበት ነው የሚባለው የሶሪያ ጉዳይም ከዚህ ጨዋታ የዘለለ አይደለም። ለችግሩ መፍትሄ በሚል የቀረበው ረቂቅ የውሳኔ ሀሳብ፣ በቻይና እና በራሺያ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ውድቅ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ የበሽር አላሳድ መንግስትን የሚደግፉት ቻይና እና ራሺያ፣ የውሳኔ ሀሳቡ መንግስትን ብቻ በመኮነን ተቃዋሚ ሀይሎችን በዝምታ ያለፈው በዚሁ የውሳኔ ሀሳብ በመሆኑ ድምፃቸውን መንፈጋቸውን ይገልፃሉ፡፡ በመንግስታቱ ድርጅት የራሺያ አምባሳደር ቪታሊ ቸርኪን የአገራቸውን ውሳኔ አስመልክቶ ተጠይቀው በሰጡት አስተያየት፣ የውሳኔ ሀሳቡ ሁሉንም ወገኖች በእኩል የሚኮንን ሳይሆን የአላሳድን መንግስት በተናጠል የሚኮንን በመሆኑ አገራቸው ልትቀበለው እንደማትችል ተናግረዋል፡፡
አፍሪካ፤ ጃፓን፤ ህንድ እና የብሪክስ አገሮች የፀጥታው ምክር ቤት አሰራር ላይ የማሻሻያ ለውጥ እንዲደረግ ከሚጎተጉቱ አገሮች እና አካባቢያዊ ድርጅቶች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ አሁን ባለው አሰራር የብዙሀንን ጥቅም ማስከበር እንደማይቻል በተለያዩ ማስረጃዎች አስደግፈው ያቀርባሉ። ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዳይሆን ቢደረግም ሆነ አገሮች እና አካባቢያዊ ድርጅቶች የመብቱ ተጠቃሚ መሆን ቢችሉ እንኳን፣ የራስን ጥቅም ማስላትን አያስቀርም፤ መጠላለፉን ከማወሳሰብ በስተቀር የሚሉም አሉ፡፡

Published in ከአለም ዙሪያ

“...ሀገራችን ፀሐይ ወጥቶ! አሁንማ ፀሐይ ወጥቶልናል። ሆስፒታላችን ከተሰራልን ወዲህ ምን ችግር አለ... ሞትማ እንዲህ በቀላሉም አይደፍረን፡፡ መቼም ነብስ የእግዚሀር ናትና ሲያበቃላት መትረፊያ የላትም እንጂ... እንዲህ በምኑም በምኑም አልጋ መያዝማ ቀርቶአል፡፡ ይኼው አሁን እኔን ከበሽታ ነጻ አውጥቶኛል፡፡ እዚህ ጉያዬ ስር አንድ ሕመም ነበረብኝ... ፍልፍል አድርጎ አውጥቶ ወርውሮልኝ... ይኼው አሁን ነጻ አውጥቶኛል፡፡ ሐኪሙም አየለ የሚባለው ዶ/ር ነው...”
ከላይ ያነበባችሁት በመርሐቤቴ አለም ከተማ እናት ሆስፒታል ያገኘናቸው አባወራ እማኝነት ነው፡፡ መርሐቤቴ በአማራው ክልል የምትገኝ ስትሆን ከአዲስ አበባ በጎጃም መንገድ መካጡሪ ከተማ ሲደረስ ወደ ቀኝ በመታጠፍ ወደ /111/ አንድ መቶ አስራ አንድ ኪሎ ሜትር ጥርጊያ መንገድ ተገብቶ የምትገኝ ነች፡፡ መርሐቤቴ ተራራማ ስትሆን ዠማ የሚባል ወንዝ መሐል ለመሐል የሚጉዋዝባት እጅግ አስደናቂ ተፈጥሮአዊ ውበት ያላት ናት፡፡ በእርግጥ ከስድስት አመት በፊት መንገዱ እንዲህ በዋዛ የማይደፈር ሲሆን አሁን ግን ዳገት ቁልቁለቱ እንዳለ ቢሆንም ጥርጊያው በማማሩ በጥንቃቄ መንዳት እንጂ እንደቀድሞው ሰውን ማሰቃየቱ አብቅቶአል፡፡ እንደሀገሬው ተስፋም ብዙም ሳይቆይ ወደ አስፋልትነት ይቀየራል፡፡ ግራና ቀኙን እያዩ የተራራውን አቀማመጥ፣ ተፈጥሮአዊ ሀብቱን እያደነቁ ከአንዱ ተራራ ወደአንዱ እየተ ዙዋዙዋሩ ሲጉዋዙ ድካሙን ሳያስቡ ከመርሐቤቴ አለም ከተማ ይደርሳሉ፡፡ አለም ከተማ መሐል አደባባይ ላይ አንድ ልጅ የታቀፈ ሰው ሐውልት ያያሉ፡፡ ቀረብ ብለው ሲያጣሩ ምስሉ የሜንሽን ፎር ሜንሽን መስራች የዶ/ር ካርል ሄንዝ ቦም  ነው፡፡ ሜንሽን ፎር ሜንሽን በመርሐቤቴ ከሰራቸው የልማት ስራዎች መካከል እናት ሆስፒታል አንዱ ሲሆን በመሀል ከተማው አደባባይ ላይ የሚገኘው ሐውልት ለአስተዋጽኦው ማስታወሻ ሐገሬው ለመስራቹ ዶ/ር ካርል ያቆመለት ሐውልት ነው፡፡ እኛም ፈልገን የተጉዋዝነው እናት ሆስፒታልን ነውና በመጀመሪያ የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ የሰጡትን ማብራሪያ ለንባብ እንላለን፡፡
“...እኔ አቶ ደነቀ አየለ እባላለሁ፡፡ በዚህ ሆስፒታል ቀደም ሲል የጤና መኮንን ሆኜ የሰራሁ ስሆን አሁን ደግሞ ስራ አስኪያጅ ነኝ፡፡ በአለም ከተማ እናት ሆስፒታል የተሰራው በሜንሽን ፎር ሜንሽን አማካኝት ሲሆን የመሰረት ድንጋዩ እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1991 ዓ/ም ተጥሎ በ1996 ዓ/ም በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እና በሆስፒታሉ መስራች ዶ/ር ካርል ሄንዝ ቦብ ተመርቆ ህብረተሰቡን በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡
ጥ/ ሆስፒታሉ እናት ሆስፒታል የተባለበት ምክንያት ምንድነው?
መ/    የሆስፒታሉ መጠሪያ እናት እንዲሆን የተወሰነው በመስራቹ በዶ/ር ካርል ነው፡፡ ይኼውም የመሰረት ድንጋይ በሚጣልበት ወቅት ለሚሰራው ሆስፒታልም ስም እንዲወጣ ህብረተሰቡ ተነጋግሮ ሁሉም ለምርጫ የሚሆነውን ስም በልቡ ይዞ ነበር ወደስፍራው የተሰበሰበው፡፡ ከወጣው ህብረተሰብ መካከልም ህጻናትም ይገኙ ነበር፡፡ ከህጻናቱ መካከል አንዲት በዝቅተኛ ደረጃ ከሚኖሩ ቤተሰቦች የተወለደች ልጅ በጣም ቆሽሻ፣ በዝንብ ተወርራ በሚያሳዝን ሁኔታ ቆማ ነበር፡፡ ዶ/ር ካርልም ከልጆቹ መካከል ብድግ አድርገው አቅፈው እያዘኑ ከተመለከቱዋት በሁዋላ ስሙዋ ማን እንደሆነ ጠየቁ፡፡ ስሙዋ እናት መሆኑ ሲነገራቸው  ...በቃ ሆስፒታሉ እናት ተብሎአል ብለው ወሰኑ፡፡ በጊዜው ህብረተሰቡ በተለያዩ  ስሞች ላይ ውይይት አድርጎ የነበረ ስለሆነ ለምን በሚል ቅር ቢለውም ውሳኔው በመወሰኑ ሆስፒታሉ እናት ሆስፒታል ተብሎ ተሰይሞአል፡፡ ልጅቱም በሰዎች ለሰዎች ድርጅት ከነቤተሰቦችዋ እየተረዳች ትምህርቷን እንድትቀጥል ተደርጎአል፡፡
ጥ/    ሆስፒታሉ ደረጃው ምንድነው?
መ/    አለም ከተማ እናት ሆስፒታል ደረጃው በመጀመሪያ ደረጃ ወይንም በወረዳ ደረጃ ዲስትሪክት ሆስፒታል ሆኖ የሚሰራ ነው፡፡ ከአካባቢው አቀማመጥ ጋር ተያይዞ ሌላም ተመሳሳይ የጤና ተቋም ባለመኖሩ በአካባቢው የሚኖሩ ወደ 250‚000 /ሁለት መቶ ሀምሳ ሺህ/ የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማገልገል ላይ ነው፡፡ ከሌሎች አጎራባች ክልሎች ወይንም ዞኖች ...ለምሳሌ ከኦሮሞ የሚመጡትንም ተገልጋዮች አካቶ በርካታ ሰዎችን እያገለገለ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት ወደ /158/ አንድ መቶ ሀምሳ ስምንት ሰራተኞችን የያዘ ሲሆን በተለይም ባለሙያዎችን በሚመለከት ከአምስት በላይ ዶክተሮች እና አንድ የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት ስለሚገኝ ከደረጃው በላይ እየሰራ ነው ማለት ይቻላል፡፡
ዶ/ር አየለ ተሸመ በአለም ከተማ እናት ሆስፒታል የማህጸንና ጽንስ ሐኪምና የሆስ ፒታሉ  ሜዲካል ዳይሬክተር ናቸው፡፡
ጥ/ ዶ/ር አየለ መርሐቤቴን ለስራ ከመመደብ ውጭ አስቀድሞ ያውቁዋታል?
መ/ እኔ ተወላጅነቴም እድገቴም በዚሁ በመርሐቤቴ ነው። አሁን የምኖርበት ቤት ቀደም ሲል ጤና ጣቢያ የነበረና እኔም የተወለድኩበት ማዋለጃ የነበረ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ከህክምና ትምህርት ቤት ተመርቄ እንደወጣሁ በጠቅላላ ሐኪምነትም የሰራሁት በዚሁ ሆስፒታል ነው፡፡ ከዚያም ለአራት አመት ያህል ከ2000-2004 እንደገና ስፔሻላይዜሽን ተምሬ በመመለስ የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት በመሆን በማገልገል ላይ እገኛለሁ፡፡
ጥ/  ምደባው በአጋጣሚ ነው ወይንስ በምርጫ?
መ/ እኔ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ትምህርት ቤት በጥቁር አንበሳ የመጀመሪያ ዲግሪዬን ስማር የማህጸን መፈንዳት ሪፖርት ሲደረግ ብዙዎች ከመርሐቤቴ የሚመጡ መሆናቸው የሚነገር ነበር፡፡ በጊዜው መንገዱ እጅግ አሳዛኝ እና አስቸጋሪ ስለነበር እንዲሁም የሚፈለገው ሕክምና በጊዜው በአካባቢው ካለው የጤና ጣቢያ አቅም በላይ የሆነ ችግር ስለሆነ ወላዶች በጣም ይሰቃዩ ነበር፡፡ በእርግጥ የሰዎች ለሰዎች ድርጅት አምቡላንስ ይሰጥ ስለነበር ወደአዲስ አበባ እንዲደርሱ የሚደረግ ቢሆንም ከመዘግየት የተነሳ ረጅም ጊዜ በምጥ በመቆየት ሴቶቹ ይጎዱ ነበር፡፡ እናም አንዳንድ ጊዜ የጠዋት ሪፖርት ላይ የማህጸን መፈንዳት ደርሶአል ሲባል ከየት ከመርሐቤቴ ናት? እስከማለት ድረስ መነጋገሪያ መሆኑ በጣም ያሳዝነኝ ነበር፡፡ በእርግጥ ካለው ዘርፈ ብዙ የጤና ችግር ምክንያት አንባቢው በጤና ጣቢያ ደረጃ ባለበት ጊዜም ሶስት እና አራት ሐኪሞች ይመደቡ የነበረ ቢሆንም ሐኪሞቹም በዚህ የመቆየት ፍላጎት ስለሌላቸው እና ከጤና ጣብያው አቅምም ጋር በተያያዘ በተለይም ለወላዶች በቀላሉ የማይፈቱ የጤና ጠንቆች ይገጥሙዋቸው ነበር፡፡ ስለዚህ እኔም ትምህርቴን ልጨርስ እንጂ በዚያ ገጠራማ ቦታ ገብቼ ህብረተሰቡን ማገልገል አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡ መጀመሪያ ላይ ምንም እንኩዋን ጠቅላላ ሐኪም ብሆንም የእናቶችን ችግር ስለማውቅ ከሰዎች ለሰዎች ድርጅት ጋር ተነጋግሬ ለሶስት ወር ለወላዶች የድንገተኛ ቀዶ ሕክምና ስልጠና አግኝቼ በማዋለድ ተግባር ላይ እንድሰማራ እራሴን አዘጋጀሁ፡፡ ከዚያም ከኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር በተገኘው እድል እንደገና ለስድስት ወር ባለሙያዎችን አሰልጥኜ እኔም ስራዬን እዚሁ ቀጠልኩ፡፡
ጥ/ በገጠር ሆስፒታል ውስጥ እስፔሻሊስት ይመደባልን?
መ/ በጀት ስለሌለ የገጠር ሆስፒታል ውስጥ እስፔሻሊስት አይመደብም፡፡ እናም የጤና ቢሮው እምቢ ቢልም ከዚህ የስራ አመራር ቦርድና ሽማግሌዎች ሄደው በማስፈቀዳቸው እና የእኔም ፍላጎት ስለነበረበት እንድመደብ ተደርጎ በመስራት ላይ ነኝ፡፡
ዶ/ር አየለ ተሸመ በስራቸው ያጋጠማቸውን እንዲህ ሲሉ አውግተዋል፡፡
“...አንዲት ሴት በምጥ ተይዛ በቤቷ ትቆይና ልጇን ትገላገላለች፡፡ ነገር ግን እንግዴ ልጁ እምቢ ስላለ ወደሆስፒታል ያመጡአታል፡፡ ሴትየዋ በሞት እና በህይወት መካከል ነበረች። ስለዚህም እንግዴልጁን ለማውጣት መጀመሪያ የደም ልገሳ እንደሚያስፈልግ ስንነግራቸው እንዴት ተደርጎ የሚል ነገር ተነሳ፡፡ እኛም ምንም ችግር የለውም አልንና... ባለቤቷን...
አንተ ባለቤቷ አይደለህም? አልነው... ነኝ የእርሱ መልስ ነበር፡፡ ታድያ ሚስትህ ከምትሞት አንተ ደም ስጥ... ስንለው  ...አረግ …እኔማ ገበሬ ነኝ ከየት አምጥቼ ነው ለእሷ ደም የምስጥ? መልሱ ነበር፡፡
በመቀጠልም እናትየውን አነጋገርን፡፡
አረግ ...እኔማ ልጄ ብትሞት አልሻም፡፡ ነገር ግን ...እኔ አሮጊት ነኝ ደም ከወዴት አመጣለሁ? ለእኔም አልበቃኝ... መልሳቸው ነበር፡፡ አብረው የነበሩትም ይልቁንም ሳትሞት ይስጡን እና እንውሰድ፡፡ ከሞተች መውሰጃውም አይገኝ ወደሚል ውይይት ገቡ፡፡ እኛም አይናችን እያየ እንዳትሞት ተነጋገርንና ሰዎቹን አስወጥተን ...አንድ ሰራተኛና አንድ አስታማሚ ደም ሰጥተው ህይወቷን አተረፍናት፡፡
ከዚያም ያ ደም የለገሰ ሰውየ ተናደደና ወደሰዎቹ በመሄድ ...ሴትየይቱ  እኮ ሞታለች ...ለምን አስከሬኑን አትወስዱም ሲላቸው... ከተማይቱ እስክትናወጥ ድረስ ኡኡታቸውን አቀለጡት፡፡ በሁዋላም በሉ ዝም በሉ ...እሱዋ ድናለች ሲባል ተደሰቱ፡፡  ከዚያም ወደህብረተሰቡ ሄደው ምስክርነታቸውን ሲሰጡ ለካንስ ይኼም አለ በሚል አሁን ደም የሚለግሱ ሰዎች ማህበር ተቋቁሞአል፡፡ ወደ ሁለት መቶ የሚደርሱ ሰዎች የደም ልገሳ ማህበርተኞች ሆነው ተመዝግበዋል፡፡ ስለዚህም ሰዎቹ የደም አይነታቸው፣ የሚኖሩበት አካባቢ፣ የስልክ ቁጥራቸው ተመዝግቦ የሚገኝ ስለሆነ አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ካሉበት ድረስ አምቡላንስ እየላክን እንጠራቸዋለን፡፡ ከሰራተኞቹም እኔን ጨምሮ ፈቃደኞች የሆንን በየሶስት ወሩ ደም እንሰጣለን። እናት ሆስፒታል የደም ባንክ ባይኖረውም አስፈላጊው የላቦራቶሪ ስራ እየተሰራ ለተጠቃሚዎች ደም ይሰጣል፡፡ በእርግጥ ከአዲስ አበባም ደም ባንክ የተቻለውን ያህል ደም ቢሰጠንም በቂ ስለማይሆን ከህብረተሰቡ የሚደረግልን እገዛ ችግሩን አስቀርቶልናል፡፡ ይህም ጥሩ ተሞክሮ ስለሆነ ለሌሎች እንደምሳሌ የሚነሳ ሆኖአል፡፡
ይቀጥላል፡፡

Published in ላንተና ላንቺ
Page 1 of 13