የፕሬዚደንት ግርማ የ60 ዓመት የአገልግሎት ዘመን ይከበራል
በመጪው ዓመት መስከረም ወር መጨረሻ ላይ የሥልጣን ዘመናቸውን የሚያጠናቅቁት የኢፌዲሪ ፕሬዚደንት የተከበሩ ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የ89 ዓመት ልደትና የስልሳ ዓመት የስራ ዘመን አገልግሎት በዓል የፊታችን ማክሰኞ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲሁም አምባሳደሮችና ታዋቂ ሰዎች በተገኙበት በሸራተን አዲስ እንደሚከበር ተገለፀ፡፡ከአፄ ኃ/ሥላሴ ዘመን ጀምሮ እስካሁን ድረስ በሶስት መንግስታት በተለያዩ የስራ ኃላፊነቶች ላይ እያገለገሉ የቆዩት ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፤ ‹‹ለሃገር መስራትን የመሰለ ክብር ያለው ነገር የለም›› ይላሉ፡፡
ሃዊ ቴክኖሎጂ የመቄዶኒያ አዛውንቶችን ለገና ምሳ ያበላል
ሃዊ ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያ የተባለው የቻይና ኩባንያ የገና በዓልን አስመልክቶ የፊታችን ሰኞ ለመቄዶኒያ የአዛውንቶች እንክብካቤ ማዕከል የምሳ ዝግጅትና ልዩ ስጦታ እንዳዘጋጀ ገለፀ፡፡ የሃዊ ቴክኖሎጂ ሰራተኞች የገና በዓልን ከማዕከሉ አዛውንቶች ጋር እንደሚያከብሩ የገለፀው ኩባንያው፤ ከምሳ ግብዣው በተጨማሪ ለአዛውንቱ ፍራሽ፣ ብርድ ልብስ፣ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣ ጤፍና የአዋቂ ዳይፐር እንደሚበረከትላቸው ለማወቅ ተችላል፡፡ መቄዶኒያ የአዛውንቶች እንክብካቤ ማዕከል ጧሪ የሌላቸውንና ታመው በየመንገዱ የወደቁ አዛውንትን ሰብስቦ ድጋፍ የሚያደርግ የበጎ አድራጎት ተቋም ነው፡፡
“የጅብ እርሻ ነገር ሳያድግ በቡቃያው”
“ሕዝቦች የስልጣን ባለቤቶች ናቸው፡፡ የምርጫው ውጤትም በእጃቸው ላይ ነው፡፡ እናም ሁላችንም የምርጫ ካርድ እንውሰድ፡፡ ምርጫው ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሐዊ እንዲሆን የበኩላችንን ጥረት እናድርግ፡፡ ምርጫ ዘጠና ሰባት ያሳየንን የሕዝብ ጉልበት በተግባር ላይ እናውለው፡፡ አሁንም ከተደራጀንና በነቂስ ለምርጫ ከወጣን----ማሸነፍ በእጃችን ያለ አማራጭ መሆኑን አንዘንጋ---”
ከሙሼ ሰሙ (የኢዴፓ ፕሬዚደንት)
በአንድ ወቅት ወደ ሰሜን ሸዋ ለቅስቀሳ ከተላከው የቅንጅት አመራር ቡድን ጋር ተመድቤ ቅስቀሳውን ካጠናቀቅን በኋላ፣ ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር የመወያየት እድል ገጥሞኝ ነበር፡፡ በቅስቀሳው እጅግ ደስተኛ የነበሩት አርሶ አደሮችን ማንን ትመርጣላችሁ ለሚለው ጥያቄ የሰጡኝ መልስ “ቅንጅትን” የሚል ነበር፡፡
የሆስተሷን አይን አጥፍቷል የተባለው በይግባኝ 20 አመት ተፈረደበት
ከፍተኛው ፍ/ቤት 14 አመት ፈርዶበት ነበር
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ አስተናጋጅ የነበረችውን ሆስተስ አበራሽ ሀይላይን አይን አጥፍቷል ተብሎ ከፍተኛ ፍ/ቤት የ14 ዓመት እስር በይኖበት የነበረው የቀድሞ ባለቤቷ ፍስሃ ታደሰ፤ አቃቤ ህግ ለጠቅላይ ፍ/ቤት ባቀረበው ይግባኝ ትላንትና የ20 አመት እስር ተፈረደበት፡፡ ለጠቅላይ ፍ/ቤት ባቀረበው ይግባኝ የስር ፍ/ቤት የህግ ስህተት አለበት ያለው አቃቤ ህግ፤ ተከሳሹ ጋብቻቸው
በፍቺ ከተጠናቀቀ በኋላ ሆን ብሎ ሰው ለመግደል ማሰቡ፣ የእድሜ ታናሹንና የቀድሞ ባለቤቱን በአሰቃቂ ሁኔታ ለመግደል መሞከሩ፣ ድርጊቱን መፈፀሜን አላስታውስም ብሎ በመካድ መከራከሩ እንዲሁም በተለያዩ የሰውነት ክፍሎቿ ላይ የፈፀመው ጉዳትና ድርጊት ሲታይ የስር ፍ/ቤት የሰጠው ውሳኔ አነስተኛ መሆኑን ይጠቁማል ብሏል፡፡
የቀድሞ ባለቤቱን ጨምሮ 4 ሠው የገደለው ተጠርጣሪ አልተያዘም
በሠሜን ሸዋ ዞን መርሃቤቴ ወረዳ ልዩ ስሙ ጭራሮ ማርያም በተባለ ቦታ የቀድሞ ባለቤቱን ጨምሮ የባለቤቱን ወላጅ እናት፣ ወንድም እና የትዳር ጓደኛዋን በጥይት ደብድቦ የገደለው ተጠርጣሪ እስካሁን እንዳልተያዘ ተገለፀ፡፡ ተጠርጣሪው ታህሳስ 11 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡30 ገደማ ነው ግድያውን የፈፀመው ተብሏል፡፡ በእለቱ በተፈፀመው ግድያ ወላጅ እናታቸውን ወ/ሮ ዘነበች አደፍርስን፣ ወንድማቸውን አቶ ችሮታው መኮንንን እንዲሁም እህታቸውን ወ/ሮ አበሬ መኮንን እና ባለቤቷን አቶ ተጫነን በአንዲት ጀንበር ያጡት አቶ አሻግሬ መኮንን፤ ይህን ሁሉ ሠው የገደለው ግለሠብ እስካሁን በፖሊስ ቁጥጥር ስር አለመዋሉ የፈጠረባቸውን ስጋት በመግለፅ ወደግድያ ላመራው ጠብ መነሻ የሆነው የንብረት ክፍፍል ጉዳይ መሆኑን ገልፀውልናል፡፡
የኢሬቴድ ድርጅት ም/ዋና ዳይሬክተር በጠ/ሚኒስቴር ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ
የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ሰለሞን ተስፋዬ ተሊላ፤ በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የአስተዳደርና ፍትህ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ፡፡ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በትያትር ጥበብ የመጀመርያ ድግሪያቸውን ያገኙት አቶ ሰለሞን፤ በጠ/ሚ ጽ/ቤት የተመደቡበት ሃላፊነት ከፍትህና ከአስተዳደር አካላት ለጠ/ሚኒስትሩ የሚመጡ ሪፖርቶችንና ሰነዶችን መመርመርና
ሙሉ አጭር መግለጫ ማዘጋጀት፣ እንዲሁም የማጣራት ስራን ያካትታል፡፡ በመምህርነት የሰሩት አቶ ሰለሞን፤ በደቡብ ክልል ማስታወቂያ ቢሮ በኃላፊነት፣ በደቡብ ክልል መገናኛ ብዙሃን በስራ አስኪያጅነት ያገለገሉ ሲሆን በ1998 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሬዲዮ የሬዲዮ ዘርፍ ስራ አስኪያጅ የነበሩ ሲሆን ኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ሲዋሀዱ በምክትል ዋና ዳይሬክተርነት ተሾመው ሲያገለግሉ እንደቆዩ ታውቋል፡፡
በአራት ኪሎ ዩኒቨርስቲ በተቀሰቀሰ ብጥብጥ ተማሪዎች ተጎድተዋል
የኦሮሞ ብሔር ተወላጆችን የሚነቅፍ ፅሁፍ በግድግዳ ላይ ተፅፎ ተገኝቷል
ፖሊስ መንስኤውን እያጣራሁ ነው ብሏል
ባለፈው ረቡዕ በአራት ኪሎ ዩኒቨርስቲ የወንዶች ዶርም ግድግዳ ላይ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆችን የሚነቅፍ ፅሁፍ ተፅፏል በሚል በተቀሰቀሰ ብጥብጥ፣ በበርካታ ተማሪዎች ላይ ጉዳት እንደደረሰ ምንጮች ተናገሩ፡፡ ፖሊስ የብጥብጡን መንስኤ እያጣራሁ ነው ብሏል፡፡ ምንጮች እንደገለፁት፤ በወንዶች ዶርም ግድግዳ ላይ የተፃፈውን የኦሮሞ ብሔር ተወላጆችን የሚነቅፍ ፅሁፍ ቀድሞ ያየው ተማሪ ለግቢው ፖሊስ ያመለከተ ሲሆን ፖሊሱም የተፃፈውን ፅሁፉ ወዲያው ያጠፋው ቢሆንም ፅሑፉ በሌላ ቦታ ላይም በመገኘቱ፣ ለብጥብጥ መነሻ ሆኗል ተብሏል፡፡
ታህሳስ ፡ የበርካታ አማልክት የልደት ቀን
ለግብፅም ሆነ ለአውሮፓና ለኤሺያ ታህሳስ ልዩ ትርጉም አለው
ብርድ ወደ ሙቀት፤ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሸጋገሪያ ወር ነው
ታህሳስ 16 (ዲሰምበር 25)፡ “ፀሐይ የምትወለድበት ቀን” ነው
ዲሰምበር 25 ቀን የልደት ቀን የሚከበርላቸው አማልክት
ናዝራዊው ኢየሱስ፣ የፔርሻው ሚትራ፣ የግብፁ ሖረስ፣ የግሪኮቹ ዲየኒሰስ፣ የቱርክ አቲስ
ሁሉም የአምላክ ልጅ አምላክ ተብለው ይመለካሉ።
ሁሉም ከድንግል የተወለዱ እንደሆኑ ይታመንባቸዋል።
ሁሉም ሞተው ተነስተዋል - ብዙዎቹ በሶስተኛው ቀን።