ልብ-ወለድ

Friday, 15 April 2022 16:18

ትናንቴ ተከተለኝ

Written by
Rate this item
(2 votes)
አለሌ ነበርኩ። ከህንድ እስከ እብድ የቀረኝ የለም የምል አለሌ። የተኛኋቸው ሴቶች ጠቢቡ ሰለሞን ከተኛቸው የሚያንሱ አይደለም፤ አልቆጠርኳቸውም እንጂ።ጀንጅኜ መዳረሻዬ ማራኪ ሆቴል ነው። ሆቴሏ ሸጎጥ ያለች ሰዋራ ስፍራ ነች፤ ከመኖርያዬ በርቀት የምትገኝ። አስተናጋጆቹ ምቹ ናቸው። በእርግጥ ጉርሻ ምቹ የማያደርገው የለም። ፈረንጁና…
Saturday, 02 April 2022 12:02

የዚያን ቀን...

Written by
Rate this item
(3 votes)
ከስራ እንደወጣሁ ሻወር ወስጄ ቺፕሴን አቀራርቤ፣ ሪሞት አንስቼ ልክ ፊልሜን ሳስጀምር... አንድ ወታደር ብቻ የምትመራው ጄነራሏ ፍቅረኛዬ ደወለች።"ላይብረሪ ውስጥ እያየሁህ አይደለም!" አለችኝ እንዳነሳሁት። መርህ ትወዳለች። መርህ አልባ ሰው ደግሞ ትጠላለች። እኔም ከሷ እኩል ለመሔድ ከአባቱ ጋር ገበያ እንደሚሔድ ህፃን በሶምሶማ…
Saturday, 26 March 2022 15:47

“ውራጅ”

Written by
Rate this item
(1 Vote)
"-+መኪናዋን ስንመለስም እየነዳት ነበር፡፡ ከእኔ ይልቅ ከመኪናዋ ጋር ክፉ ትዝታ ያለበት ይመስላል፡፡ እኔን ከአልጋው ቤት ከወጣን በኋላ አልነካኝም፡፡ እኔ ደግሞ በተገላቢጦሽ ላቅፈው እፈልጋለሁ፡፡ አልተያዘልኝም፡፡ ያሟልጫል፡፡ ዝም ብዬ አለቅሳለሁ፡፡ የማለቅሰው ለራሴ ነው፡፡--" ምድርን ከሰዎች ጋር እጋራለሁ፡፡ ግን፣ አስታዋሽ ካልመጣብኝ መርሳት የምፈልገው…
Saturday, 19 March 2022 11:50

ጐዳናዉ

Written by
Rate this item
(6 votes)
"--ማሕሌትን የመክሊትን ያህል ባልቀርባትም የምንጋራዉ ተመሳሳይ ታሪከ ስላለን ብቻ አዝንላታለሁ፡፡ ማሕሌት ሀሜት ልብሷ ነዉ፤ እሷን እኔ ፊት የሚያማ ሴት ግን የለም፡፡ አብዛኛዉ የቡና ቤት ወሬ በግለሰቦች ታሪክ ላይ የሚሽከረከር ነዉ፡፡ መነሻዉም መድረሻዉም የሌሎች የተሸሸገ ጀርባ ነዉ፡፡ የቡና ቤት ሴት እንደ…
Saturday, 05 March 2022 12:55

የመጀመሪያይቱ

Written by
Rate this item
(8 votes)
ሌሊቱ ቀኑን ሊተካ ተካልቦ፣ ጀምበሯ ወርቃማ ቡሉኮዋን ተከናንባ አድማሱ ላይ ተንሰራፍታለች፡፡ የተጎለትኩበት ባሕር ዳርቻ፣ ከዳር እስከ ዳር ጀምበሯ በምትፈነጥቀዉ ጮራ ተጥለቅልቋል። አካባቢዉ ላይ የሚገኘዉ ነገር ሁሉ ወርቃማ መልክን ይዞ የተፈጠረ ይመስላል። አሸዋዉ፣ አለቱ፣ ባሕሩ፣ ከርቀት የሚታዩት ጎብኝዎችን ጭነዉ ባሕሩ ላይ…
Tuesday, 01 March 2022 00:00

ሐመልማል

Written by
Rate this item
(4 votes)
 እነሆ በአርባ ቀን እድል ፈንታዬ እግር ብረት እንደተጠፈርኩ ዘመን ገስግሶ ሰላሳኛ አመቴን ደፈንኩ፡፡ የሚበቃኝን ያህል ዘመን ኖሬአለሁ፡፡ መኖር ዐቢይ ፋይዳ የሌለዉ ከንቱ ጉዞ ነዉ፡፡ አድካሚዉ የሕይወት ጉዞዬ በሞት ሲቋጭ ገላዬ የምስጥ ሲሳይ ይሆናል፡፡ ከዛ እንደማንኛውም ተራ ሰው ሳልውል ሳላድር እረሳለሁ፡፡…
Page 8 of 65