ልብ-ወለድ
(ከ“ACRES OF DIAMONDS!” ….. ዶ/ር ራሴል ኮንዌል በጥቂቱ ተሻሽሎ የተተረጎመ፡፡) ልቤ በዚህች በምጎበኛት አገር ማለለ፤ ወደድኳት። በርሃ ብትሆንም ቅሉ፣ በርሃ ውበት እንዳለው ማየት የቻልኩት አሁን ነው፡፡ በልቤም ‹ከጉብኝቴ መልስ ወደ አባት አገር አልመለስም› ስል ማልኩ! እዚህ ሰርቼ መለወጥ እችላለሁ፡፡ አገሬ…
Read 3587 times
Published in
ልብ-ወለድ
በህይወታቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ልጃቸው በቴሌቪዥን እንደሚታይ ተነግሯቸው አፍጥጠው እየጠበቁ ነው፡፡ በዚያ ላይ ሰሞኑን በጎረቤታቸው ልጅ ሞት ምክንያት ሀዘን ስለተቀመጡ ድምፁን መቀነስ ግድ ብሏቸዋል፡፡ ወሬውን የነገረቻቸው የሰፈራቸው ልጅ አስካለ ናት፡፡ አስካለ ደግሞ ፈጣንና ዘመናዊ ስለሆነች ትታመናለች፡፡ ስለዚህ ቴሌቪዥኑን አስተካክላ አብረው አፈጠጡ፡፡…
Read 2175 times
Published in
ልብ-ወለድ
ስንጋባ ከለምለም ከንፈሮችዋ የሚፈልቀው የፍቅር ቃል፣ ልብ የሚያስለመልመው ቅላፄዋ ሁሉ ማርኮኝ ነበር፡፡ በተለይ የሽፋሽፍቷ ግርማ፣ ያይኖችዋን ብርሃን እየከለለ ሲያቀብለኝ፣ የገነት በሮች ወለል ብለው የተከፈቱልኝን ያህል ተደንቄ ነበር፡፡ የሰርጋችንም ቀን ያ ውበትዋ፣ በቬሎ አሸብርቆ ብቅ ሲል፣ ነፍሴ ክንፎችዋን አራግፋ፣ በዝማሬ ዜማ…
Read 3122 times
Published in
ልብ-ወለድ
ስለታመሙ፣ ስለደከሙ፣ ሞተው ስለተቀበሩ አገር ጥለው ስለጠፉ፣ በየበረሃውም ነፍሳቸውንስለገበሩ፡፡ (ብቻም ሳይሆን፣ ስለ ራሳችሁም ጸልዩ!)* * *አዲስ አበባ … /እኛ ሰፈር/ከስድስት አመት በፊት፣ አንድ ዕለት እንደተለመደው ሲኒማ ገብቼ ስመለስ አንደኛው ጓደኛዬ ድንገት ጠራኝና እንዲህ አለኝ፤ ‹‹…እኛ ብሩን አግኝተናል አንተ ብቻ ነህ…
Read 2449 times
Published in
ልብ-ወለድ
ድንገት በአንዲት ደሴት ላይ ነቃሁ፡፡ እውነቱን ለመናገር፣ ልንቃ ወይስ ልተኛ እርግጠኛ አይደለሁም። የመንቃትና የመተኛት ልዩነት፤ በነጭና በሌላ ነጭ መሀል ያለ ዓይነት ልዩነት ሆኖ ነው የሚሰማኝ፡፡ ደሴቲቱ ቅልብጭ ያለችና ብዙ ኮተቶችን ያልያዘች ናት፡፡ ለጸሐይ መውጫና መጥለቂያ የሚያገለግሏት የምሥራቅና የምዕራብ አቅጣጫዎች ብቻ…
Read 2661 times
Published in
ልብ-ወለድ
ትናንትና የእናቴን ሁለተኛ ሙት ዓመት ተዝካር አወጣሁ፡፡ ከዚህ ወር መግቢያ ጀምሮ በተደጋጋሚ በህልሜ እየመጣች ስታስጨንቀኝ ነበር፡፡ ተዝካሯን እንዳወጣላት ማስታወሷ እንደሆነ ገብቶኛል!፡፡ ግና የሙት ዓመቴን ይረሳዋል ብላ በማሰቧ በጣም ተናድጃለሁ፡፡ እናቴ ትሙት በጣም ታዝብያታለሁ። በርግጥ እናቴም ቢሆን እውነት አላት፡፡ ደሞዜን የተቀበልሁ…
Read 2617 times
Published in
ልብ-ወለድ