ኪነ-ጥበባዊ ዜና
በገጣሚ ኤፍሬም ስዩም የተዘጋጀው “ተዋናይ ብሉይ የግዕዝ ቅኔያት ፍልስፍና ከቀደምት የኢትዮጵያ ነገስታትና ሊቃውንት” የተሰኘ መጽሐፍ በሚቀጥለው ሳምንት አርብ ከ11 ሰዓት ተኩል ጀምሮ በጣልያን የባህል ተቋም እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ ውርስ ትርጉሙ በኤፍሬም ስዩም የተዘጋጀው መጽሐፉ፤ በሚመረቅበት ዕለት ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋና መጋቢ ሃዲስ…
Read 2016 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
በሚካኤል ልኡልሰገድ የተዘጋጀው “የፊልም ጽሑፍ አፃፃፍ” የተሰኘ መጽሐፍ ዛሬ ከቀኑ 9፡30 በጣይቱ ሆቴል ጃዝ አምባ እንደሚመረቅ ፕሮግራሙን በትብብት ያዘጋጀው አላቲኖስ ፊልም ሰሪዎች ማህበር በላከው መግለጫ አስታወቀ፡፡ ሚካኤል ልኡልሰገድ “የማትበላ ወፍ” የተሰኘው ፊልም ደራሲና ዳይሬክተር መሆኑ ይታወቃል፡፡
Read 1908 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
በ1997 ዓ.ም ተጀምሮ በየአመቱ እየተካሄደ ያለው “የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫል” ስምንተኛ ዝግጅት ባለፈው ሰኞ ምሽት በብሔራዊ ትያትር በሚደረግ የሽልማት ሥነሥርዓት እንደሚጠናቀቅ ሊንኬጅ አርት ሪሶርስ ሴንተር አስታወቀ፡፡ ዝግጅቱን የሚያቀርበው የሊንኬጅ አርት ዋና ሥራ አስኪያጅ አርቲስት ይርጋሸዋ ተሾመ ለአዲስ አድማስ እንደገለፀው፣ በፌስቲቫሉ…
Read 3153 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
ሚዩዚክ ሜይዴይ “አመኛው ክልስ” በተሰኘው የዳንኤል ሁክ መጽሐፍ ላይ ነገ ውይይት እንደሚካሄድ ገለፀ፡፡ ከቀኑ 8 ሰዓት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመጻሕፍት የሚካሄደውን የሦስት ሰዓታት ውይይት፣ የመነሻ ሀሳብ በማቅረብ የሚመሩት የሥነ ጽሑፍ ባለሙያው አቶ አስቻለው ከበደ ናቸው፡፡
Read 2311 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
“አቦል፣ ቶና፣ በረካ” በሚል ርእስ ቡና ላይ ያተኮረ የሥዕል አውደርእይ እንደሚቀርብ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ በመጪው አርብ በአምስት ኪሎው ብሔራዊ ቤተመዘክር ተከፍቶ እስከ ታህሳስ 7 ለሕዝብ በሚቀርበው አውደርእይ የሚገኘው ገቢ፣ ቦንጋ ላይ ለሚገነባው የቡና ቤተመዘክር ሕንፃ ማሰሪያ እንደሚውል አዘጋጆቹ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
Read 2502 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
መሳይ ፕሮሞሽን ከመንሱር ጀማል ፕሮሞሽን ጋር በመሆን የፀረ “የፆታ ጥቃት” ዘመቻ ቀንን የተመለከተ ኪነጥባዊ ዝግጅት ትናንት ጠዋት በሀገር ፍቅር ትያትር ቤት አዳራሽ አቀረበ፡፡ “እኔንም ይመለከተኛል” በሚል መሪ ቃል በቀረበው ዝግጅት ግጥሞች፣ ወግ፣ መነባንብ፣ ሙዚቃዊ ድራማ እና ሥነቃሎች ቀርበዋል፡፡
Read 1744 times
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና