ልብ-ወለድ
እነሆ የባቢሌ የመሞቻ ቀን ደረሰ፡፡ ደረሰና ተገነዘ፡፡ ወደ ጉድጓድ ተወረወረ፡፡ ከጉድጓድ በስቲያ ምስጥና ጉንዳን በልቶ የተረፈው ነፍሱ ወደ ሚቀጥለው ምዕራፍ ተሰደደ፡፡ የሚቀጥለው ምዕራፍ የሚወሰነው እንደ ሟቹ እምነት ነው፡፡ ባቢሌ ከሞት በኋላ መንግስተ ሰማይ ወይንም መንግስተ ሰይጣን ይኖራል ብሎ የሚያምን በመሆኑ…
Read 6104 times
Published in
ልብ-ወለድ
…. ወተት በበራድ ከመጣዴ፣ በሩ ተንኳኳ፡፡ “ይግቡ” ከማለቴ ጐረቤቴ በሩን ገፋ አድርጐ ብቅ አለ፡፡ ግንባሩ እንደ ጥይት የሾለ፤ ካውያ ራስ፡፡ ወደ ክፍሉ እንድመጣ አጣደፈኝ፡፡ ‘ምን ገጠመው’ በሚል ተከትየው ወደክፍሉ ገባሁ፡፡ “ተቀመጥ… የማነብልህ ጽሑፍ አለኝ”…“ይቅርታ መቆየት አልችልም… ወተት ጥጄ ነው የመጣሁት፤…
Read 4750 times
Published in
ልብ-ወለድ
የዛሬው ቀን ልዩ የሚያደርገው ፀጉሬን የምቆረጥበት ቀን በመሆኑ ነው፡፡ ፀጉር ቆራጩ ሁሌ ሶስት ወራት ቆይቼ ስለምመጣ ይረሳኛል፡፡ ምን አይነት ቁርጥ እንደሚስማማኝ ትዕግስት ወስጄ ማስረዳት ይኖርብኛል፡፡ ትልቅ ገለፃ የሚያስፈልገው የጭንቅላት ቅርፅም ሆነ የፀጉር አይነት የለኝም፡፡ ያው ያድጋል----መታጨድ አለበት ነው ዋናው ቁም…
Read 3910 times
Published in
ልብ-ወለድ
አቶ ወንዳፍራሽ እኚህ ፍራሽ አዳሽ የዋዛ ሰው እንዳይመስሉዋችሀ፡፡ ሰለሞን ራሱ ከጥበቡ ቆንጥሮ የሰጣቸው ሰው ናቸው፡፡ አሁን ይኸ ልጃቸው አዝብጤ፣ ከነስሙም አዝብጤ በአምስት ዓመቱ የአንድ ሙሉ ሰራተኛ ሥራ ሲሰራላቸው ይውላል፤ የኔታ ትምህርት የለም ያሉ ለታ፡፡ እንግዲህ በፍራሽ ሥራና እደሳ የሚኖሩ እንደሚያውቁት…
Read 3737 times
Published in
ልብ-ወለድ
ስለዚህች ሴት ለማሰብ የምችለው ከእኔ ርቃ ስትሄድ ብቻ ነው፡፡ አጠገቤ እያለች ስለሷ ለማሰብ አልችልም፡፡ አንድን ነገር በደንብ ለማየት እንዲቻል ነገርዬው ከርቀት መሆን ይኖርበታል፡፡ ከርቀት ሲኮን ነው የእውነት የሚገለፀው፡፡ የምን ነገር ማወሳሰብ ነው?!በቃ አሁን እቺ ሴት ትዝ እያለችኝ ነው፡፡ ቤቱ ውስጥ…
Read 6522 times
Published in
ልብ-ወለድ
… ከዛ ደግሞ አያፍርም… ቤቴ መጥተህ ካልዋልክ ብሎ ማጅራቴን አንቆ ወሰደኝ፡፡ ሁለት መኝታ ቤት ያለው አፓርትመንት ውስጥ ነው የምኖረው ብሎኝ ነበር፡፡ አፓርትመንቱ ኮንዶሚኒየም መሆኑን ሳይ .. ይኼ ልጅ ውሸታም ነው ለካ ብዬ በቅሬታ ገላመጥኩት፡፡ ምናልባት የነገረኝ ሌሎች ነገሮችም ውሸት ሳይሆኑ…
Read 4604 times
Published in
ልብ-ወለድ