Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 22 December 2012 11:12

የልጆች መፃህፍት በአማርኛና በኦሮምኛ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

ባለፈው ሳምንት እሁድ በኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል በተካሄደ የመፃህፍት ምረቃ ስነ ስርዓት ላይ 12 መፃህፍት ተመረቁ፡፡ የመፃህፍቱ ደራሲ አበባ ሽታዬ እንደገለፀችው፤ አንደኛው “ብርቱ ሰልፍ” የተሰኘ የግጥም መድበል ሲሆን አስራ አንዱ ደግሞ በአማርኛና በኦሮምኛ የተዘጋጁ የህፃናት የተረትና የትምህርት መርጃ መፃህፍት ናቸው፡፡ የግጥም መድበሉ በ20 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን የህፃናት መፃህፍቱ ከ10ብር-15ብር እየተሸጠ እንደሆነ ታውቋል፡፡ ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ ከተካሄደው የመፃህፍቱ ምረቃ ሁለት ሳምንት ቀደም ብሎ በአምቦ ተመሳሳይ ምረቃ እንደተደረገ ደራሲዋ ተናግራለች፡፡

Read 5016 times