አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የደቡብና ሰሜን ቀጠና አስተባባሪዎችን መድቦ ትናንት ሽኝት አደረገ፡፡
የፓርቲው ህዝብ አደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ ኢንጅነር ዘለቀ ረዲ ትናንት ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ ፓርቲው አገሪቱን አዲስ አበባን ጨምሮ በአምስት ቀጠናዎች በመከፋፈል የህዝብ አደረጃጀቱንና የማስተባበር ሥራውን ለመሥራት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ በዚሁ መሰረት በሰሜን እና በደቡብ ቀጠናዎች ህዝቡን የማደራጀትና የማስተባበር ሥራ እንዲሰሩ ሁለት ኃላፊዎችን መድቦ፣ ወደ ቦታው የላከ ሲሆን አቶ ግርማ አማረን ለደቡብ ቀጠና፣ አቶ አዕምሮ አወቀን ደግሞ ለሰሜን ቀጠና አስተባባሪነት በመመደብ ትናንት ሽኝት አካሂዷል፡፡ ይህም በአገሪቱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ታሪክ ከዚህ ቀደም ያልተደረገና አዲስ አሰራር ነው ብለዋል፡፡