ወርሃዊ የሥነ ፅሁፍ ዝግጅቱን የፊታችን ሰኞ ከምሽቱ 12 ሰአት ጀምሮ በራስ ሆቴል እንደሚያቀርብ ዩሴ የማስታወቂያ ድርጅት አስታወቀ፡፡ በዝግጅቱ ላይ አርቲስት አዳነች ወልደገብርኤል፣ ገጣሚ ባየልኝ አያሌው፣ ገጣሚት ትዕግስት ማሞ፣ ተዋናይና ወግ ፀሐፊ ፍቃዱ ከበደ፣ ድምፃዊት ጠረፍ ጥላሁን (ኪያ)፣ ገጣሚ ሰለሞን ሳህለ እና አርቲስት ሄኖክ በሪሁን የስነፅሁፍ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡
በተመሳሳይ ዜና፣ ግጥም እና ሙዚቃ ተዋዝተው የሚቀርቡበት “ግጥምን በጃዝ” 17ኛ ምሽት ዝግጅቱን የፊታችን ረቡዕ ምሽት በራስ ሆቴል ትልቁ አዳራሽ ያቀርባል፡፡