Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 10 September 2011 13:53

..ሁሉም የሥራውን ፍሬ የሚያገኝባት ሀገር እመኛለሁ..

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በ2003 ዓ.ም ጥበብ አድጓል አላደገም የሚለውን ለመናገር ብዙ ነገሮች ያስፈልጋል፡፡ ጠቅለል አድርገን ስናየው በርካታ ፊልሞች በመሠራታቸው ከሆነ፣ በብዙ መንገድ በርካታ ፊልሞች እየወጡ ይገኛል፡፡ በዚህ ረገድ ሙያው ትኩረት እየተሰጠው እያደገ መሆኑን እናያለን፡፡ ተዋናዩ የተሻለ ነገር የሚያሳይና ተዋናዩን ያከበረም ነው፡፡ ይሄንን ዕድገት ለማስቀጠል በበኩሌ እኔ ፕሮዲዩስ የማደርገው የራሴ ድርሰት ለማቅረብ፣ ከጓደኞቼ ጋር አዲስ ፊልም ለማበርከት እየተሯሯጥኩ ነው፡፡ በአገሪቱ ተከሰተ የምለው አስደሳችና አስቸጋሪ ለይቼ የማየው የተለየ ነገር የለም፡፡ በ2004 ዓ.ም መልካም ወሬ የሚወራባት፤ ሰው አብሮ ተባብሮ በቀናነት የሚተያይባት፤ ሁሉም የሥራውን ፍሬ የሚያገኝበት፤ የተሻለ ለውጥ የምናይበት ሀገር እንድትሆን እመኛለሁ፡፡
ሜሮን ጌትነት
ገጣሚ እና ተዋናይ

Read 5395 times