Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 08 December 2012 10:59

ባታ ጫማ ለአገራችን ገበያ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

አበሻ የባህል ማዕከል እና የስዕል ጋለሪ ከባታ ጫማ አምራች ኩባንያ ጋር በመዋዋል የባታ ምርት የሆኑትን ጫማዎች ለአገራችን ገበያ ከዛሬ ጀምሮ ያቀርባል፡፡ በአለማችን ከአምስት ሺህ በላይ የሚሆኑ ወኪል ሱቆች ያሉት የባታ ጫማ አምራች ኩባንያ የሴትና የወንድ የህፃናት እና የአዋቂ ጫማዎችን ከ80 ብር እስከ 1800 ብር በሚደርስ ዋጋ ለአገራችን ገበያ ለማቅረብ ከአበሻ ጋለሪ ጋር በወኪልነት መፈራረሙን የጋለሪው ባለቤትና ስራ አስኪያጅ አቶ በድሩ ሙዘይን ተናግረዋል፡፡

አቶ በድሩ እንደተናገሩት ባታ ጫማዎች ከፍተኛ ስም ያላቸው እና በአለም ደረጃ ተቀባይነት ያላቸው ሲሆን በአውሮፓ እና በአሜሪካ የሚመረቱ ናቸው ብለዋል፡፡ የጫማዎቹ ጥራቶች በአውሮፓ ደረጃ ተሠርተው ይዞታቸውን ሳይቀይሩ ወደ አገራችን እንደሚገቡ ገልፀው አንዳንዴ ስም ብቻ በመያዝ ጥራቱ የቀነሰ ጫማዎች በውድ ዋጋ ለገበያ እንደሚቀርቡ ገልፀው የባታ ጫማ ምርቶች ግን በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራታቸውን እንደጠበቁ ለገበያ ይቀርባሉ ይላሉ - አቶ በድሩ ለዚህም ሲባል በሽያጭ ማዕከል ውስጥ የሚሠሩትን ሠራተኞች በኬንያ ማሠልጠኑን የተናገሩት ስራ አስኪያጁ ለማሳያነት ዛሬ በፒያሳ በሚከፈተው የሽያጭ ማዕከላት ስራውን እንደሚጀምር ገልፀው፤ በቀጣይ በክልል እና በተለያዩ የአዲስ አበባ ከተሞች የመሸጫ ማዕከሎች እንደሚኖሩ እና በቀጣይም የጀመሩትን የፋብሪካ ግንባታ በማጠናቀቅ የባታ ጫማዎችን በአገራችን ለማምረት መታሰቡን ገልፀዋል፡፡

 

Read 4796 times Last modified on Saturday, 08 December 2012 11:04