የግጥም ሥራዎች ከጃዝ ሙዚቃ ጋር ተዋህደው የሚቀርቡበት ..ፖየቲክ ጃዝ.. የፊታችን ረቡዕ ጳጉሜ 2/2003 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡30 ጀምሮ በሸበሌ ሆቴል እንደተዘጋጀ ተገለፀ፡፡በዝግጅቱ ላይ ገጣሚና ጋዜጠኛ አበባው መላኩ፣ ገጣሚና ሰዓሊ ቸርነት ወ/ገብርኤል፣ ገጣሚ ምስራቅ ተረፈና ገጣሚ ሰለሞን ሳህለ ከመለከት ባንድ ጋር የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡ የአሁኑ ዝግጅት ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑን የጠቆሙት አዘጋጆቹ፤ ፕሮግራሙን በየወሩ ለማቅረብ ከሸበሌ ሆቴል ባለቤት ፈቃድ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡