ሀገሬ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን እና እቴጌ ምንትዋብ አርት ፕሮሞሽን የሚያስተባብሩትን ዝክረ ይርጋን አስመልክቶ የሀገሬ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሄኖክ ስዩም ..ከያንያን አዝማሪ በሚባሉበት ዘመን መስዋእትነት ከፍለው የሀገሪቱን ማህበረሰብ ሙዚቃ በማሳደጋቸው ሀገራዊ አስተዋኦዋቸውን በማሰብ ዝግጅቱ ቀርቧል.. ካሉ በኋላ የአርቲስቱ አልባሳትና ቁሳቁስ በቋሚነት ቤተመዘክር ከፍቶ ለማስቀመጥ እንደታሰበ ጠቁመዋል፡፡
ከአርቲስት ባህሩ ቃኜ እና አርቲስት ራሄል ዮሐንስ ጋር ባቀነቀነው ..የሰው የለው ሞኝ.. በሚለው ዘፈኑ የሚታወቀው አርቲስት ይርጋ ዱባለ በኢትዮ-ሶማሊያ ጦርነት ወቅት ባወጣው ..የፍየል ወጠጤ.. የተሰኘ ዘፈኑ ይታወቃል፡፡
ከዚህም ሌላ በፕሮፌሰር ሃይሌ ገሪማ መመረቂያ ፊልም ..3ሺህ ምርጦች..፣ እና ..ሻፍት ኢን አፍሪካ.. ፊልሞች በተዋናይነት ተሳትፏል፡፡
የድምፃዊው ቀብር ..አርበኛ እንጂ ሙዚቀኛ አይደሉም በጀግና ሥርዓት ይቀበሩ.. በሚል ውዝግብ ፈጥሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡