Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 13 August 2011 10:52

አርቲስቶች ለምስራቅ አፍሪካ ረሃብ ዘመቻ ጀምረዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የቦብ ማርሌይ ፋውንዴሽን ለኢትዮጵያ 100ሺ ዶላር ለገሰ
በአፍሪካ ቀንድ ባሉ አገራት የሚገኙ 12 ሚሊዮን የረሃብ ተጠቂዎችን ለመታደግ ከ150 በላይ የዓለም ምርጥ አርቲስቶች በኢንተርኔት ሶሻል ሚዲያ የገቢ ማሰባሰብ ዘመቻ መጀመራቸውን የቢልቦርድ መሄት ዘገበ፡፡   ከ60 ዓመታት በኋላ የከፋ ረሃብ በምስራቅ አፍሪካ ከወር በፊት የተከሰተ ሲሆን በተለይ በሶማሊያ ረሀቡ 3.6 ሚሊዮን ህዝብ እንዳጠቃና በኬንያና በኢትዮጵያም ረሃቡ እየተስፋፋ መምጣቱን ያመለከተው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ነው፡፡

በሶሻል ሚዲያ በተጀመረው ዘመቻ ..አይአምጎ ነቢዩር ፍሬንድ.ኦርግ.. በሚል ድረ ገ በ1973 እ.ኤ.አ የተዘፈነው የቦብ ማርሌይና ዘ ዌለርስ ..ሃይ ታይድ ሎው ታይድ.. የተሰኘው ዜማ ከኢንተርኔት ለሚገለብጡ አድማጮች በ1.29 ዶላር የቀረበ ሲሆን በዘመቻው 1 ቢሊዮን የዓለም ህዝቦችን ለማስተባበር ታቅዷል፡፡ በዚሁ የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴ ቢዮንሴ፣ ማዶና፣ ብሪትኒ ስፒርስ፣ ሌዲ ጋጋ፣ ፖል ማካርቲኒ፣ ጀስቲን ቢበርና ሌሎቹም የዓለማችን ምርጥ ሙዚቀኞች እየተሳተፉ ናቸው፡፡ በተያያዘ የቦብ ማርሌይ ቤተሰብ ..ዋን ላቭ.. በተባለው ፋውንዴሽን ..ሰላማዊ፣ ንፁህና የተሟላ የወደፊት ዓለማችንን እንፍጠር.. በሚል መርሁ 100ሺ ዶላር ለኢትዮጵያ እንደለገሰ ታውቋል፡፡ ፋውንዴሽኑ ሰሞኑን በለገሰው የገንዘብ እርዳታ 1300 መንደሮች፤ 12 ክሊኒኮችና 128 ትምህርት ቤቶችን የንፁህ መጠጥ ውሃ  ተጠቃሚ እንዳሚያደርግ ተገልል፡፡

 

Read 3557 times Last modified on Saturday, 13 August 2011 11:00