Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Monday, 08 August 2011 09:31

ፊፍቲ ሴንት ሃብታምነት ነፃነት ሰጥቶኛል አለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በሙሉ ስሙ ከርቲስ ጃክሰን ተብሎ የሚጠራው ጥቁር አሜሪካዊው ራፐርና የፊልም ተዋናይ 50 ሴንት፤ ..ሃብታም መሆኔ ነፃነት ሰጥቶኛል.. ሲል ለፋይናሻል ታይምስ መጽሔት ተናገረ፡፡ ..ቺታሪ ቪዥን.. የተባለ የፊልም ኩባንያ በ200 ሚሊዮን ዶላር ያቋቋመው ፊፍቲ ሴንት፤ ሙዚቃውን ወደ ጐን በመተው በፊልም ስራ መጠመዱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በሁለት ዓመት ውስጥ 10 ፊልሞች ለመስራት ያቀደው ፊፍቲ ሴንት፤ በቅርቡ ..ቲንግስ ፎል አፓርት.. የተሰኘ አዲስ ፊልሙን ለዕይታ ያበቃል፡፡ ራፐሩ በፊልም ኩባንያው አማካኝነት ከብሩስ ዊልስ፣ ዲኔሮና ከሌሎች ታላላቅ ተዋናዮች ጋር እየሠራ መሆኑን ዘ ፋይናንሻል ታይምስ አትቷል፡፡የ36 ዓመቱ ፊፍቲ ሴንት የመጀመሪያ የሙዚቃ አልበሙን ከ8 ዓመት በፊት ለገበያ ያበቃ ሲሆን እስካሁን ያወጣቸው አልበሞች ከ25 ሚሊዮን ቅጂዎች በላይ በዓለም ዙሪያ ሸጧል፡፡

 

Read 5591 times Last modified on Monday, 08 August 2011 09:35