በአርቲስት ታምሩ ብርሃኑ የተዘጋጀው “ባለሥልጣኑ” የተሰኘው ፊልም ነገ እና ማክሰኞ እንደሚመረቅ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ በፊልሙ ላይ ታምሩ ብርሃኑ፣ ሱራፌል ተካ፣ ሃና ዮሐንስ፣ አበበ ተምትም፣ ወለላ አሰፋ፣ ታጠቅ ነጋሽ፣ ፍቅርተ ጌታሁን እና ሌሎችም ተውነዋል፡፡ ፊልሙ ነገ በአዲስ አበባ የግል ሲኒማ ቤቶች እና በመንግስታዊው የስቴርዮ ሲኒማ በዋነኛነት ደግሞ ማክሰኞ ምሽት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር እንደሚመረቅ ተገልጿል፡፡