Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 10 November 2012 13:49

ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ 42 ሚ. ብር ማትረፉን አስታወቀ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ባለፈው ዓመት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ ሕይወት ነክ ካልሆነው የኢንሹራንስ ሥራ 336 ሚ ብር፣ ከሕይወት ኢንሹራንስ ደግሞ 13.53 ሚ ብር በአጠቃላይ 349.53 ሚ ብር የአረቦን ገቢ በማስመዝገብ ከታክስ በፊት 42 ሚ. ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ፡፡ ህዳር 10 ቀን 2012 ዓ.ም 10ኛ ዓመት በዓሉን የሚያከብረው ኩባንያው፤ የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪውን ከተቀላቀለበት ጀምሮ ባለፉት 10 ዓመታት በካፒታል በኢንቨስትመንት፣ በሀብት መጠን፣ በቅርንጫፍ ስርጭት፣ በየዓመቱ በሚያስገባው የአረቦን ገቢና ትርፍ፣ በፈጣን አገልግሎት አሰጣጥ ዕድገት እያስመዘገበ የቆየ ኩባንያ መሆኑን የጠቆመው ኩባንያው፤ የኢንሹራንስ የገበያ ድርሻውን 9.1 በመቶ በማሳደግ የኢንዱስትሪውን የገበያ ድርሻ ከሚመሩት ኩባንያዎች አንዱ መሆኑን ገልጿል፡፡ ኩባንያው በዚሁ በጀት ዓመት ሕይወት ነክ ባልሆነው የኢንሹራንስ ዘርፍ 136.54 ሚ ብር፣ ለሕይወት ኢንሹራንስ ደግሞ 7.1 ሚ ብር በአጠቃላይ 143.67 ሚ ብር ካሣ መክፈሉን አስታውቋል፡፡ ለካሣ ጥያቄ ከተከፈለው ገንዘብ ውስጥ 69.5 በመቶ የሸፈነው ከተሽከርካሪ አደጋ ጋር በተያያዘ ሲሆን፤ ከሕይወት ኢንሹራንስ ደግሞ ለሕክምና ወጪ የተከፈለው ካሣ 82 በመቶ ድርሻ እንደነበራቸው ገልጿል፡፡በአሁኑ ጊዜ የኩባንያው የተጣራ ሀብት 268.7 ሚ. ብር፣ የተከፈለ ካፒታሉ 65 ሚ. ብር ሲሆን የባለአክሲዮኖች ብዛት 866 መድረሱ ታውቋል፡፡

Read 3858 times

Latest from