Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 10 November 2012 13:45

ዋሽንግተን ተቀምጬ አሜሪካ ናፈቀችኝ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

አብሮ ሲወጣ አይታይም ወይም አንድም ሰው ዘመድ መጥቶ ሲወስደው አይታይም፡፡ እኔ እደተረዳሁት አሜሪካ ሁለተኛ አገራችሁ ናት›› አለችኝ፡፡  ይኸኛው ግን የእኔም ጥያቄ ነበር፡፡ ዋሽንግተን ኢትዮጵያ ሆናብኛለች፡፡ ከኢትዮጵያ ሳልወጣ የናፈቀችኝ አሜሪካ አሁንም እንደናፈቀችኝ ነው፡፡ አገር ማለት ሕዝብ ነው፤ ዋሽንግተን ደግሞ ኢትዮጵያዊ ይበዛል በአማርኛ እያሰበ፣ በአማርኛ እያወራ፣ በአማርኛ የሚኖር ሕዝብ ነው ያለው፡፡ ታዲያ እንዴት አትናፍቀኝ!  ‹‹እናንተ አገር ትምሕርት እና ሥራ የለም?›› ወተወተችኝ ‹‹አለ ግን እዚህ የተሻለ ትምሕርት እና የተሻለ ሥራ ስለሚያገኙ ነው፤ የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቀው የሚኖሩም በርካታ ናቸው›› አልኳት፡፡ ‹‹ይሄ ሁሉ ሰው እዚህ መጥቶ እናንተ አገር ታዲያ ምን ሰው ቀራችሁ?›› አለችኝ፡፡ ‹‹እሱን እንኳን ተይው›› አልኩ በሆዴ፡፡ ‹‹እዚህ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሠርተው ራሳቸውንም አገራቸው ያለውን ቤተሰባቸውንም ይረዳሉ፤ ይህን ለማድረግ ደግሞ የተሻለ ገንዘብ ስለሚያገኙ እዚህ መሥራትን ይመርጣሉ አልኳት፡፡›› በተቻለኝ መጠን ስለሁኔታው ላስረዳት ሞከርኩ፡፡

‹‹የአገራችሁን ኢኮኖሚ በባላ ደግፈው የያዙት እነዚህ ናቸዋ፡፡ በተዘዋዋሪ በአሜሪካ እየተረዳችሁ ነው ማለት ነው›› ወይ ድፍረት! ማን ይገላግለኝ ከዚህች ሴት! አሜሪካ በስደት ላይ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን ብቻ አለመሆናችንን ላስረዳት ሞከርኩ፡፡ ‹‹ለምሳሌ እኛን ያቀፈው ቡድን ከ17 አፍሪካ አገራት የመጣን ጋዜጠኞችን የያዘ ነው፡፡ግን አንድም ሰው እንዳንቺ ይህን ያህል ሰው ሰላም ሲል፡፡ ስለ ባሕላችን አጫወትኳት ‹‹ግን ይህ ሁሉ የአገራችሁ ሰው እንዴት መጣ? እዚህስ ምን ይሠራል? እኔ አሁን እዚህ ከመጣሁ አንድ የአገሬን ሰው አላገኘሁም›› አለችኝ፡፡ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ለሥራ እና ለትምሕርት እንደሚመጣ ነገርኳት፡፡አንድ የሕንጻው ጠባቂም አብሮ ቆሟል - ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡ ሰላም አልኳቸው፡፡ ቦትሷናዊቷ ጓደኛዬ ግራ በመጋባት ጠየቀችኝ ‹‹ዲሲ ከመጣን ጀምሮ የምታገኛቸው ኢትጵያውያን ብዙ ናቸው፤ ሁሉም ሰላም ይሉሻል፣ ይጋብዙሻል አገርሽ ታዋቂ ነሽ እንዴ?›› ታዋቂ እንዳልሆንኩ እና ሰላም የምላቸውን ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንደማላውቃቸው ነገርኳት፡፡ ‹‹ሳትተዋወቁ እንዴት ሰላም ትባባላላችሁ?›› አለችኝ፡፡ ከዳውን ታውን  ፔንታገን ወደተባለው የገበያ ሥፍራ ዕቃ ለመግዛት የሄድኩት እንደኔው ከቦትስዋና ከመጣች ጋዜጠኛ ጋር ነበር - በባቡር፡፡ ባቡሩ ውስጥ አምስት ኢትዮጵያውያንን ሰላም አልኩ፡፡ ወደ ገበያ ማእከሉ ስንገባ የአዲስ አበባውን ፍሬንድሽፕ ሕንጻ አስታወሰኝ፡፡ ኢትዮጵያዊ ወጣት ነጋዴዎች የተለያዩ እቃዎች ይሸጣሉ፡፡ በየመንገዱ የማገኛቸው ኢትዮጵያውያን እንግሊዘኛ ከማውራትም ከባይተዋርነት ገላገሉኝ፡፡ ዋሽንግተን መጥቶ እንግሊዘኛ የመልመድ ወይም የማውራት ፍላጎት ያለው ኢትዮጵያዊ ካለ ሲያምረው ይቀራል፡፡ አማርኛ በዋሽንግተን የሥራ ቋንቋ ይመስላል፡፡ ከአነስተኛ ቦታ እስከ ከፍተኛ ቦታ የሚሠሩ፤ ከለምኖ አዳሪ እስከ ሚሊዬን ዶላር የሚቆጥሩ ኢትዮጵያውያን በዲሲ እና ዙሪያዋ ይገኛሉ፡፡ በተለይ ቨርጂኒያ ውስጥ ‹‹ጎጃም በረንዳ›› እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ ይኖራሉ፡፡ ከዚህ ቀደም ስለዚህ አካባቢ በወሬ በወሬ ሰምቼ የነበረ ቢሆንም እውነት አይመስለኝም ነበር፡፡ ያገኘሁት ግን ከሰማሁት በላይ ነው፡፡ እንደውም በዚህ አካባቢ አንድ ሌላ አሜሪካዊ ቢታይ ሰው አገር ተሰዶ የመጣ ሊመስል ይችላል፡፡ እያንዳንዱ ሱቅ የተለጠፈው ማስታወቂያ በሙሉ የተጻፈው በአማርኛ ነው፡፡ አከራረሜ እንዲህ ከሆነ መልሴን በመቅረጸ ድምጽ አስቀርቼ ገና ሲጠይቁኝ እየከፈትኩ ማሰማት ሳይሻለኝ እንደማይቀር ገመትኩ፡፡ ግን ደግሞ አሳዘኑኝ፡፡ አዲስ የመጣ ሰው ሲያገኙ ስለአገራቸው ለማወቅ መጓጓታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡ ዋሽንግተን ዲሲ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ብትሸትም ከኢትዮጵያ የመጣ ሰው ይናፍቃቸዋል፡፡ የዋሽንግተንን የታክሲ ሥራ ቀጥ አድርገው የያዙት ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡ አብረውኝ ያሉት አፍሪካውያን እንኳን አንድ ነገር ሲፈልጉ ‹‹እባክሽ የአገርሽን ሰዎች ጠይቂልን›› ይሉኝ ጀመር፡፡ ከሬስቶራንቱ ወጥተን ወደ ሆቴሉ ለመመለስ ያስቆምነው ታክሲ ሹፌር ኢትዮጵያዊ ነው እሱም አዲስ መሆኔን ሲያውቅ ያንኑ ጥያቄ ደገመልኝ፤‹‹አገር ቤት እንዴት ነው?›› ደህና መሆኑን ነገርኩት ‹‹ትመለሻለሽ?›› በአንድ ቀን  የጥያቄው ተመሳሳይት አሰለቸኝ፡፡ ጓደኛዬ ትንሽ ዞር ዞር አድርጋ ከታማውን ካሳየችኝ በኋላ “ላሊበላ” ወደ ተባለ የኢትዮጵያውያን ሬስቶራንት ይዛኝ ሄደች፡፡ወደ ውስጥ ስገባ አነስተኛዋ የሬስቶራንቱ ውስጠኛ ክፍል በሰው ተሞልታለች፡፡ ባንኮኒው በበርካታ አዛውንት ኢትዮጵያውያን ተከቧል፡፡ አብዛኞቹ ጊዮርጊስ ቢራ ይጠጣሉ፡፡ እንጀራ የያዙ ትሪዎች በተመጋቢዎቻቸው ፊት ተቀምጠዋል፡፡ በቀኝ በኩል ከተቀመጡ ሦስት ነጮች በስተቀር ቤቱን ግጥም አድርጎ የሞላው ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ጓደኛዬ ለምታውቃቸው ሰዎች ሰላምታ ሰጥተን ወንበር ይዘን ቁጭ አልን፡፡አንድ ወዳጇም እንደኛው ወንበር ስቦ አብሮን ቁጭ አለ፡፡እሱም አዲስ መሆኔን ሲያውቅ አገር እንዴት እንደሰነበተ ቀደም ካሉት ጋር ተመሳሳይ ጥያቄ አቀረበልኝ፡፡ ቀሪ መሆን አለመሆኔንም ጨምሮ ጠየቀኝ፡፡ ምክር ቢጤም ለገሰኝ፡፡ የቀረበልንን ጎድን ጥብስ ከዚህ ቀደም ኢትጵያ ውስጥ አንድም ቦታ እንዳልበላሁት እርግጠኛ ነኝ፡፡እንጀራው ጨው ጨው ከማለቱ ውጪ ጥብሱ በጣም ጣፋጭ ነበር፡፡ ጨዋታችን እስከ እኩለ ሌሊት ቀጠለ፡፡ ሬስቶራንቱን ለቅቄ ወጥቼ የዲሲን ሕንጻዎች እስመለከት ድረስ ያለሁት አሜሪካ መሆኑን ለማመን ተቸገርኩ፡፡አብዛኞቹ ወጣት ናቸው፡፡ ከ50 ዓመት በላይ የሚሆናቸውም አሉ፡፡ ከሰዓታት ቆይታ በኋላ የምጠብቃት ጓደኛዬ መጣችልኝና ከተማዋን ለማየት ወጣሁ፡፡ ጊዜው በጣም መሽቷል፡፡ ዳውንታውን ግን ተጨናንቃለች፡፡ ብርዱ ለእኔ ከባድ ቢሆንብኝም ዋሽንግተኖችን ግን ከእንቅስቃሴ አልገታቸውም፡፡ራሱን ካስተዋወቀኝ በኋላ ስለ እኔ ጠየቀኝ፡፡ ስገባ እንዳላየኝ ነግሮኝ የምፈልገው ነገር እንዳለ ለመተባበር ተዘጋጀ፡፡ጓደኛዬ ዘንድ ስልክ አስደወለኝ፡፡ እስክትመጣልኝም የተቀመጥኩበት ጥቂት መስተንግዶ አደረገልኝ፡፡ሁሉም እየመጡ ተራ በተራ ሰላም አሉኝ፡፡ አዲስ መጪ መሆኔን ሲያውቁ ተመሳሳይ እና ተመጋጋቢ ጥያቄ ያቀርቡልኝ ጀመር፡፡ ጥቂት ቆይቼ አንዳንድ ነገር ለመጠየቅ ወደ ታችኛው የሆቴሉ ክፍል ወረድኩ፡፡እንግዳ መቀበያው አንዱን የኢትዮጵያ ሆቴል አስታወሰኝ፡፡ረዘም ወፈር ያለች አንዲት ሴት ዩኒፎርም ለብሳ ከመሬቱ ላይ የወዳደቀ ነገር ትለቅማለች፡፡መለጥ ያለ ሰው እንግዳ መቀበያ ዴስክ ላይ ቆሞ እንግዶች ያስተናግዳል፡፡ለገቢ ወጪው በር የሚከፍቱ ሦስት ሰዎች መግቢያው ላይ ቆመዋል፡፡ወደ በሩ በኩል ወደ ውስጥ ገባ ብሎ ባለ ጠረጴዛ ላይ ወደ አራት የሚሆኑ ሰዎች ሥራ ላይ ተጠምደዋል፡፡ከውስጠኛው የሆቴሉ ክፍል ዩኒፎርም የለበሱ ሴቶች ወጣ ገባ ይላሉ፡፡ሆቴሉ ውስጥ በሚገኘው የመሸጫ ሱቅ ውስጥ አንድ ሴት እና አንድ ወንድ ቆመዋል፡፡ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡ኢትዮጵያ በሚገኝ አንድ ሆቴል ያለሁ ውስጥ ያለሁ መሰለኝ፡፡ቆሜ አካባቢውን ስቃኝ ቀድሞ ያየኝ ወደ እኔ መጣ፡፡ እንግዳ መቀበያው ጋር አራት እንግዳ አስተናጋጆች ተደርድረዋል ወደ አንደኛው ተጠጋሁ፡፡ ሻንጣውን ያገዘኝ ኢትዮጵያዊም አብሮኝ አለ፡፡”አገር ቤት እንዴት ነው? ኑሮውስ? አገራችን አድጋለች ይባላል ፖለቲካውስ?” አየር መንገድ ካገኘኋት ሴት ጋር አንድ ዐይነት ጥያቄ ጠየቀኝ፡፡ አጠር አጠር አድርጌ መለስኩለት፡፡ ክፍሌ እንደደርስኩ አመስግኜ ሸኘሁት፡፡ተቀባዮቼ እንድንሄድ ጥሪ በማድረጋቸው ተሰናብቻት ወደ ሆቴል ወደሚወስደን መኪና ጉዞ ጀመርን፡፡ ከዳላስ አየር መንገድ 40 ደቂቃ ከተጓዝን በኋላ ዋሽንግተን ዲሲ ዳውን ታውን ወደሚገኘው ሜይ ፍላወር ሆቴል ደረስን፡፡ሻንጣዬን ወደ ውስጥ የሚያስገቡልኝ የሆቴሉ ሠራተኞች ፈለግ አደረኩ፡፡ሙሉ የቀይ ቡኒ ዩኒፎርም የለበሱ እጃቸው ላይ ነጫጭ ጓንት ያጠለቁ ሁለት ሰዎች ወደኔ መጡ “እንኳን ደህና መጣሽ፤ ከአገር ቤት ነው?” ፈገግ እያልኩ በአዎንታ መለስኩላቸው፡፡እናቷን ለመቀበል ነበር የመጣችው “አገር ቤት እንዴት ነው? ኑሮውስ? አገሪቱ አድጋለች ይባላል … ፖለቲካውስ?” በጥያቄ አጣደፈችኝ፡፡  በተቻለኝ መጠን ለጥያቄዎቿ መልስ ስሰጥ ቆየሁ፡፡  አማርኛም ይሰማኝ ጀመር፡፡ ግርታ ቢጤ ተሰማኝ፡፡ሰዎቹ ሁሉንም አሰባስበው እስኪጨርሱ አንድ ቦታ ላይ ቆምኩ፡፡ አንዲት ሴት ከተቀመጠችበት መጥታ ሰላምታ ሰጠችኝ “ምነው ተቀባይ አልመጣልሽም እንዴ? ስልክ ልደውልሽው?” እንደማያስፈልገኝ ነግሬያት ጨዋታ ጀመርን፡፡ ትንሽ ጠጋ ስል ደግሞ  ሕጻናት እየተሯሯጡ ይቦርቃሉ፡፡ዐይኔን ከእነርሱ ላይ ሳነሳ የአየር መንገዱን ዩኒፎርም የለበሱ ጽዳቶች ከመሬት ላይ ቆሻሻ ይለቅማሉ፡፡ ቦሌ አየር መንገድ ያለሁ መሰለኝ፡፡የአየር መንገዱን ጣጣ ጨርሰን ተቀባይ ወዳለበት መውጫ ተጓዝን፡፡ገና ብቅ ስል አራት ኢትዮጵያውያን ጥግ ይዘው ሲያወሩ አየሁ፡፡ ስምንት ሰዓታትን በጉዞ አሳለፍኩ፡፡በመጨረሻም ቨርጂኒያ የሚገኘው ዳላስ ኤርፖርት  አመሻሹ ላይ ደረስኩ፡፡ አየሩ በጣም ቀዝቃዛ ነበር፡፡ተቀባዮቼን ገና ከአውሮፕላኑ ስወርድ አገኘኋቸው፡፡ የስም ዝርዝር ይዘው ከተለያየ ቦታ የመጣነውን ጋዜጠኞች በአንድ ላይ አሰባስበው ወደ መውጫው ወሰዱን፡፡ዋሽንግተን ዲሲ  ደንብርብር ብዬ አየሁት፤ ሳቅ አለ፡፡   ‹‹እኔም አመሰግናለሁ›› ብዬ ተሰናበትኩት፡፡ ኢትዮጵያዊ ያረገጠው መሬት የለም እያልኪ ገባሁ - አውሮፕላኑ ውስጥ፡፡  የጉዞ ሰነዴን ተቀብሎ ካየ በኋላ ‹‹እናመሰግናለን›› አለኝ ጥርት ባለ አማርኛ፡፡ እሱም የአየር መንገዱ ሠራተኛ ነው፤ በአንገቱ ሰላምታ ሰጥቶኝ አለፈ፡፡ አለፍ ስል ደግሞ ሌላውን፣ ትንሽ እንዳለፍኩ ሌላዋን አገኘሁ፡፡ ጀርመን በብርድ እና በስኖው ነበር የተቀበለችኝ፡፡ ቅዝቃዜው ወደየትም ቦታ አላንቀሳቅስ ሲለኝ ወደ አውሮፕላኑ መግቢያ ላይ ተቀምጬ ማንበብ ጀመርኩ፡፡ ከሰዓታት ቆይታ በኋላ ወደ ናፈቅኋት ዋሽንግተን የሚያደርሰኝ አውሮፕላን መጣ፡፡ መልካሙን እየተመኘ መንገደኛውን የሚሸኘው የአየር መንገዱ ወጣት ሠራተኛ የንግግር ቅላጼ ከአሜሪካኖቹ ለመለየት እጅግ ይቸግራል፡፡ መንገደኛ ይሆናል በሚል በቀስታ ዞሬ ከፈገግታ ጋር ለሰላምታው ምላሽ ሰጠሁ፡፡ሰላምታው የቀረበለኝ ከመንገደኛ ሳይሆን ከአየር መንገዱ ኢትዮጵያዊ ሠራተኛ ነበር፡፡የመጀመሪያውን የአማርኛ ሰላምታ መልሼ ትንሽ ፈቀቅ እንዳልኩ ተንቀሳቃሽ ጋሪ መሳይ ነገር ላይ የቆመ ረጅም ሰው እኔ ወዳለሁበት አካባቢ ሲመጣ ተመለከትኩ፡፡ፊቴን ወዲያ ወዲህ እያወዛወዝኩ ያየሁትን በፎቶ ለማስቀረት ካሜራዬን ደቀንኩ፡፡ወደ ምግብ እና መጠጥ መሸጫ ሱቆች አካባቢ ስደርስ በርከት ያሉ ሰዎችን ማየት ጀመርኩ ‹‹ደህና አደርሽ?›› የሚል ድምፅ ሰማሁ ለስላሳ ባለ አማርኛ፡፡የፍራንክፈርት አየር መንገድ እኛ አገር ቢኖር አቤት ስንት እና ስንት ክሊፕ ስንት እና ስንት ፊልም ይቀረጽበት ነበር ስል አሰብኩ፡፡ እንኳን ወጥቼ  ከተማውን ላይ ቀርቶ  ከመውጫዬ ወደ መግቢያዬ መድረስ አቃተኝ፡፡ አገር ለማየት ካለኝ ጉጉት የተነሳ  ሰዓቱ ምንም ሳይመስለኝ በሚያፈዘውም በማያፈዘውም እየፈዘዝኩ ረጅሙን የፍራንክፈርት አየር መንገድ በግሬ ጀመርኩት፡፡መንገዱ ረጅም ከመሆኑ የተነሳ የጠፋሁ እየመሰለኝ በመጠየቅ ልቤ ወለቀ፡፡ የአየር መንገዱ ስፋት አንድ አገር ያክላል፡፡ ለኔስ ማን መጥቶ “ውስጡን ስለማታውቀው ነው እባካችሁ አሳይሉኝ” ይበልልኝ፡፡ እያወጣሁ፤ እያወረድኩ የሚነበበውን፤ እያነበብኩ የሚጠየቀውን፣ እየጠየቅሁ ሲደክመኝ፣ የተቀመጥኩ ሲጠማኝ እየጠጣሁ ተጓዝኩ፡፡የአየርመንገዱን ጣጣ ጨርሼ ከአዲስ አበባ ዋሽንግተን ዲሲ ሊያደርሰኝ ወደተዛጋጀው አውሮፕላን ተሳፈርኩ፡፡ ከስድስት ሰዓት በረራ በኋላ ፍራንክፈርት ገባሁ፡፡ ከሉፍታንዛ ወርጄ ሁለተኛውን የዩናይትድ አየር መንገድ ለማግኘት አምስት ሰዓት ያህል መጠበቅ ነበረብኝ፡፡ ሰውየው ወደ ልጁ እየጠቆሙ “እሱ ወደ የመን ነበር የሚሄደው፤ ውስጡን ስለማያውቀው መንገድ መንገዱን ብታሳይው” አሉኝ ‹‹እኔ የምሄደው አሜሪካ እኮ ነው›› ልል አልኩና ከአፌ መለስኩት፡፡ በልቤ እፍረት ቢጤ አጠቃኝ መሰለኝ፡፡ “ችግር የለም አብረን እስከሆነው ድረስ አሳየዋለሁ፤ እኔም ባላሳየው አይጠፋውም፤ ሰውም ቢሆን ይጠይቃል” አልኳቸው፡፡ “እንደው ምንም አያውቅም፤ ከክፍለ ሐገር ነው የመጣው ብዬ ነው፡፡” አሉና ሃሳብ ገባቸው፡፡ ችግር እንደሌለው አግባብቼ አሰናበትኳቸው፡፡ ድምጹን ወደሰማሁበት ዞር አልኩ፤ ወደ ሽምግልናው መንገድ የጀመሩ ሰው ወጣት ልጅ ከጎናቸው አቁመዋል፡፡ ከኋላቸው ደግሞ ሁለት ሦስት ወጣቶች በሰውየው ጀርባ አሻግረው ዐይን ዐይኔን ያያሉ፡፡ የመንገደኞች መግቢያ ሰልፍ ውጭው ድረስ ነው፡፡ እንደምንም ዕቃ መግፊያ ጋሪ አገኘሁና ክፍት መንገድ እየፈለግሁ እንደምንም ወደ መግቢያው ተጠግቼ ቆምኩና ተራ መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ “እ…እናት እንደው አንዴ ላስቸግርሽ” ከኋላ በኩል የመጣ ድምጽ ነበር፡፡ይሳሳቃሉ፤ ይላቀሳሉ፡፡ አንድም ሰው በከተማው የቀረ አይመስልም፤ ሕጻን አዋቂው  ለስንብት በአየር መንገዱ ውስጥ ተገኝቷል፡፡ አብዛኞቹ መንገደኞች እንጀራ ፍለጋ ወደአረብ ሀገራት የሚሰደዱ መሆናቸውን ተረዳሁ፡፡ አሜሪካ መሄድ ብርቅ ሆኖብኛል፡፡መንግሥተ ሰማያትን የማየት ዕድል እንዳገኘ ሰው ፈንድቄያለሁ፡፡ ከቤቴ ተነስቼ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ስደርስ የጊቢው መኪና ማቆሚያ በሰው ተሞልቷል፡፡ መንገደኛና ሸኚው ተናንቆ ይሰነባበታል፡፡ ደስ እንዳላቸው እየተሰተሩ ማስታወሻ ለማቆየት ፎቶ ይነሳሉ፡፡

Read 5185 times