ባሳለፍነው ዓመት ብዙ አዳዲስ ሙያተኞች በመምጣታቸው ፊልም ቤቶች ከውጭ ፊልሞች ይልቅ ለሀገር ውስጥ ፊልሞች በራቸውን እየከፈቱ ነው፡፡ ከኋላዬ የመጡትን በማበረታታትና በማድነቅ ጥሩ መንገድ የማሳየት፣ ባህል ጠብቀው ሀገር ወዳድ እንዲሆኑ የማድረግ ግዴታዬንም ቀጥዬበታለሁ፡፡ የቲቢ በሽታን ለመከላከል የተሰጠኝ ኃላፊነት ከ2003 ዓ.ም የደስታ ምንጮቼ አንዱ ነው፡፡ ብዙ መሥራት በሚችሉበት ዕድሜ ድንገት ያሸለቡ ሞያተኞች ያሳዝኑኛል፡፡ 2004 ዓ.ም ኢትዮጵያውያን ሁሉ የሚደሰቱበት እንዲሆን እመኛለሁ፡፡
አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም
Published in
የሰሞኑ አጀንዳ