ከዕለታት አንድ ቀን አንድ አባት ልጁን አስከትሎ አህያ ሊሸጥ ወደ ገበያ ይወጣል፡፡
መንገድ ላይ እየተጫወቱና እየተሳሳቁ የሚመጡ ሴቶች ያገኛሉ፡፡ ሴቶቹ አባትና ልጁን እያዩ፤
..በዚህ በኮረኮንች መንገድ አህያ እያላቸው በእግራቸው የሚሄዱ ጅሎች አይታችሁ ታውቃላችሁ?.. አሉ፡፡
አባት፤ ሴቶቹ የሚሉት ትክክል ነው አለና አሰበ፡፡ ስለዚህም ልጁን አህያ ላይ ጭኖ እሱ እየተከተለ መንገድ ቀጠለ፡፡ መንገድ ላይ ሽማግሌ ጓደኞቹን አገኘ፡፡ እነሱም ..ልጅህን እንዴት እያባለግኸው እንደሆነ ታውቆሃል? አንተ ሽማግሌው በደከመህ ሰዓት ልጅህ በአህያ አንተ በእግርህ እንዴት ትሄዳለህ?.. አሉት፡፡