ሰባተኛው የአይሮቤ አሜሪካ ፊልም አውደርእይ ሰኞ ምሽት ሰሜን ሆቴል አካባቢ በሚገኘው የጣሊያን የባህል ተቋም እንደሚከፈት አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ አዲስ አበባ የሚገኙ የስፓኞልና ፖርቱጋልኛ ተናጋሪ ሀገራት ኤምባሲዎች በየዓመቱ የሚያዘጋጁት አውደርእይ እስከ ዛሬ ሳምንት ለፊልም ተመልካቾች ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡ በዚሁ መሠረት ሰኞ Un Mundo Maravilloso የተሰኘ የሜክሲኮ ኮሜዲ፣ ማክሰኞ Besouro የተሰኘ የብራዚል ድራማ፣ ረቡዕ ምሽት Habanastation የተሰኘ የኩባ ድራማ፣ ሐሙስ Oriena የተሰኘ የቬንዙዬላ ድራማ፣ አርብ Aesperanca estaonde menos se espera የተሰኘ የፖርቱጋል ድራማ እና ቅዳሜ Celda 211 የተሰኘ የስፔን ልብ አንጠልጣይ ድራማ ፊልሞች በእንግሊዝኛ ሰብታይትል ለእይታ ይቀርባሉ፡፡