በጉጉት የሚጠበቀው እና በMMA፣ Muay Thai እንዲሁም Boxing ዘርፎች የሚካሄደው የETFC 002 – Adwa Fight Night የፊት-ለፊት የፍጥጫና የሚዛን ልኬት መርሃ ግብር ዛሬ በአዲስ አበባ አድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ተካሂዷል። በዝግጅቱ ላይ ተፋላሚ አትሌቶች ፊት-ለፊት በመገናኘትና የሚዛን ልኬታቸውን በማጠናቀቅ ለዋናው የውድድር መድረክ ብቁ መሆናቸውን ያረጋገጡ ሲሆን፤ ታዋቂ አርቲስቶች፣ ቲክቶከሮች፣ ዩቲዩበሮች እና የኢንዱስትሪው አጋሮች ተገኝተዋል።
በSweat Box እና ETFC ትብብር እንዲሁም በM-Pesa፣ GoFere እና AbbayTV አጋርነት የተዘጋጀው ይህ ግዙፍ የፍልሚያ መድረክ ሰዓታት ብቻ ቀርተውታል። የፍልሚያው ትኩሳት እጅግ ከፍተኛ በሆነበት በዚህ ወቅት፣ አድናቂዎች ተጋጣሚዎቹን በድርጊት ለማየት በጉጉት እየጠበቁ የሚገኙ ሲሆን ውድድሩ ዛሬ ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 10 ሰዓት ጀምሮ በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም በድምቀት ይከናወናል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas
Thursday, 27 August 2026 12:39
ሰዓታት የቀሩት "የአድዋ ፋይት ናይት 02" የፊት-ለፊት ፍጥጫ ተካሄደ
Written by Administrator
Published in
ዜና

