Wednesday, 05 August 2026 17:20

በኃይለኛ ንፋስና ዝናብ የፈራረሱት የተፈናቃዮች መጠለያዎች በትግራይ

Written by 
Rate this item
(2 votes)
በትግራይ ክልል «ሰባ ካሬ» የተፈናቃዮች ማዕከል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተ ከባድ ዝናብ እና ኃይለኛ ንፋስ ከ20 በላይ ጊዜያዊ መጠለያዎች ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ተዘግቧል፡፡ አውሎ ነፋሱ መጠለያዎቹን ለኑሮ የማይመቹ በማድረግ የነዋሪዎችን ንብረት ያወደመ ሲሆን፤ አረጋውያንን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ህክምና ተቋማት ተወስደዋል።
ይህ አስከፊ አደጋ ቀድሞውንም አስቸጋሪ ሕይወት ለሚመሩት ተፈናቃዮች ተጨማሪ ከባድ ፈተና ሆኗል። «ጽላል» የተባለው የምዕራብ ትግራይ የህብረተሰብ ድርጅት፣ ሰብአዊ ድርጅቶች አስቸኳይ እርዳታ እንዲያደርጉ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፤ የችግሩ እውነተኛ ዘላቂ መፍትሔ ተፈናቃዮች በሰላም ወደ ቀያቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ ማመቻቸት እንደሆነ አፅንኦት ሰጥቷል።
AS-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Read 3569 times