ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወጣቶች ይህንን ክረምት ከንቱ እንዳያሳልፉ አሳስበው፣ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያላቸው የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኮርሶች ሥልጠና በነጻ እየተሰጡ መሆኑን ገለጹ። ቀደም ሲል 5 ሚሊዮን ሰዎች መመዝገባቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አሁን ደግሞ ተራው የሌሎች ወጣቶች መሆኑን በመጥቀስ ጥሪ አቅርበዋል።
በቴክኖሎጂ ዘርፍ አቅምን ለመፍጠር ትልቅ ዕድል የሆነውን ይህንን ሥልጠና ወጣቶች እንዲጠቀሙበት ያሳሰቡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ መማር የሚፈልጉ ሁሉ በድርጅቱ ድረ-ገጽ (ethiocoders.et) በመግባት አሁኑኑ እንዲመዘገቡ አሳስበዋል።
Published in
ዜና

