Wednesday, 05 August 2026 17:17

ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለወጣቶች ጥሪ አቀረቡ

Written by 
Rate this item
(0 votes)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወጣቶች ይህንን ክረምት ከንቱ እንዳያሳልፉ አሳስበው፣ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያላቸው የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኮርሶች ሥልጠና በነጻ እየተሰጡ መሆኑን ገለጹ። ቀደም ሲል 5 ሚሊዮን ሰዎች መመዝገባቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አሁን ደግሞ ተራው የሌሎች ወጣቶች መሆኑን በመጥቀስ ጥሪ አቅርበዋል።
በቴክኖሎጂ ዘርፍ አቅምን ለመፍጠር ትልቅ ዕድል የሆነውን ይህንን ሥልጠና ወጣቶች እንዲጠቀሙበት ያሳሰቡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ መማር የሚፈልጉ ሁሉ በድርጅቱ ድረ-ገጽ (ethiocoders.et) በመግባት አሁኑኑ እንዲመዘገቡ አሳስበዋል።
Read 3769 times