Wednesday, 05 August 2026 09:31

ታላቋ ባለውለታ ወ/ሮ መዓዛ ቅጣው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

Written by 
Rate this item
(2 votes)
በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር በዋና ሥራ አስኪያጅነት እና በሌሎች መሥሪያ ቤቶች ከ40 ዓመታት በላይ በታማኝነት ያገለገሉት ወ/ሮ መዓዛ ቅጣው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ወ/ሮ መዓዛ የብርሃን ኢንሹራንስ አ.ማ. መሥራችና የቀድሞ የቦርድ ሰብሳቢ የነበሩ ሲሆን፣ ለሥራቸው ትልቅ ራዕይ የነበራቸው አርአያ ሴት ነበሩ።
የብርሃን ኢንሹራንስ አመራሮችና ሠራተኞች በሕልፈታቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል። ወ/ሮ መዓዛ ኩባንያው ለዛሬው ስኬት እንዲበቃ ሌት ተቀን በትጋት በመሥራት፣ መልካም ውሳኔዎችን በማሳለፍና ትልቅ አሻራ በማሳረፍ የማይተካ ድርሻ እንደነበራቸው ተመላክቷል።
Read 2634 times