Tuesday, 04 August 2026 12:02
አክሱም ዩኒቨርሲቲ በትግራይ ክልል ባለው የጸጥታ ስጋት ምክንያት ተማሪዎቹና መምህራኑ የዝውውር ጥያቄ አቅርበዋል ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ ሲሰራጭ የነበረው መረጃ "ከእውነት የራቀ እና ምንም አይነት መነሻ የሌለው ፈጠራ ነው" ሲል አስተባበለ። ተማሪዎችና መምህራን ባልተረጋገጠ መረጃ እንዳይሸበሩ ያሳሰበው ዩኒቨርሲቲው፣ የተወራው ወሬ መሠረት የሌለው መሆኑን አረጋግጧል።
ሰሞኑን በመቀለ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ ተማሪዎችና መምህራን በትምህርት ሚኒስቴር አማካይነት ወደ ሌሎች የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲዛወሩ ጥያቄ አቅርበዋል የሚሉ መረጃዎች መሰራጨታቸው አይዘነጋም፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና

