Wednesday, 29 July 2026 19:33

“የስኮትላንድ አዲሱ ንጉሥ እሆን ይሆናል” — የኢዲ አሚን የልጅ ልጅ በቦክስ ታሪክ ለመሥራት ተዘጋጀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የቀድሞው የኡጋንዳ መሪ የኢዲ አሚን የልጅ ልጅ የሆነው አዚዝ አብዱል፣ በኮመንዌልዝ ጨዋታዎች የቦክስ ውድድር ካሸነፈ “የስኮትላንድ አዲሱ ንጉሥ” ሊሆን እንደሚችል ተናገረ። እድሜው 25 ዓመት የሆነው አብዱል በሩብ ፍፃሜው ከእንግሊዙ ዳማር ቶማስ ጋር የሚገጥም ሲሆን፣ ካሸነፈ ቢያንስ የነሐስ ሜዳሊያ የሚያገኝ ሲሆን ይህም አገሩ ኡጋንዳ ከብዙ ዓመታት በኋላ በኮመንዌልዝ ቦክስ የመጀመሪያውን ሜዳሊያ እንድታገኝ ያደርጋታል።

አያቱ ኢዲ አሚን ለስኮትላንድ በነበራቸው ፍቅር ራሳቸውን “የስኮትላንድ ንጉሥ” ብለው ይሰየሙ የነበረ ሲሆን፣ አብዱልም ያንን በማስታወስ “የስኮትላንድ አዲሱ ንጉሥ እሆን ይሆናል” ሲል ተናግሯል። አያቱ በ1950ዎቹ የታወቁ ቦክሰኛ የነበሩ ቢሆንም፣ አብዱል ግን ስለ አያቱ የፖለቲካ ታሪክ ብዙ ማውራት እንደማይፈልግና ትኩረቱ ሙሉ በሙሉ በጨዋታው ላይ እንደሆነ ገልጿል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

Read 1138 times