Tuesday, 21 July 2026 13:48

ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ ከለንደኑ ኮንሰርት መልስ መታመሙን ገለጸ!

Written by 
Rate this item
(1 Vote)
በኢትዮጵያ የሙዚቃ አድናቂዎች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ በለንደን ያቀረበውን ስኬታማ ኮንሰርት አጠናቆ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ የጤና መታወክ እንዳጋጠመው በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጹ ገለጸ።
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ባልደረባ ጋር የተነሳውን ፎቶግራፍ በማያያዝ «ታምሜ ገባሁ :: ስለሁሉ ግን እግዚአብሔር ይመስገን !!» ሲል ያሰፈረው መልዕክት በበርካታ አድናቂዎቹ ዘንድ ስጋትን የፈጠረ ሲሆን፣ ህመሙ ምን እንደሆነ በዝርዝር ባይታወቅም በርካታ ወዳጆቹ አብሮነታቸውን እየገለጹለት ይገኛሉ።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Read 8351 times