Tuesday, 21 July 2026 13:39

ኮኮዋ ከእኛ... ቸኮሌት ከአውሮፓ?!

Written by 
Rate this item
(0 votes)
"አፍሪካ በዓለም ላይ ሀብታሟ አህጉር ሆና ሳለ፣ እንዴት ወርቃችን በነጮች ይቆፈራል?
እንዴትስ አፍሪካ የአልማዝ መገኛ ሆና—ከደቡብ አፍሪካ፣ ቦትስዋና፣ ናሚቢያ፣ ሴራሊዮንና ላይቤሪያ አልማዝ እየወጣ—ዋጋውን ግን በቤልጂየም የሚገኙ ሰዎች ይወስኑታል?
ቶጎ፣ ኮትዲቯር እና ጋና ኮኮዋ ያመርታሉ፤ ነገር ግን ቸኮሌት የሚሰሩት አንድም የኮኮዋ ዛፍ የሌላቸው ስዊዘርላንድና ቤልጂየም ናቸው። ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል?
ሻይ ቅጠል በኢትዮጵያ፣ በኬንያና በኡጋንዳ ተመርቶ ወደ እንግሊዝ ሲሄድ "የእንግሊዝ ሻይ" ይባላል። ይህ እንዴት ይሆናል?
ለስልክ መስሪያ የሚያገለግለው ኮልታን የተባለው ማዕድን ከኮንጎ እየወጣ፣ አንድም የአፍሪካ ሀገር ግን ሞባይል ስልክ አያመርትም።
ይህ ሁሉ ሊሆን የቻለው አእምሮአችን እንዲማረክ በመፍቀዳችንና ማንነታችንን በመዘንጋታችን ብቻ ነው።"
(PLO Lumumba)
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Read 6736 times