ኢትዮጵያ የምታምረው በተራሮቿና በወንዞቿ ብቻ አይደለም፤ በፍቅር አብረው በሚኖሩ ዜጎቿና ሰላምን በሚተነፍሱ ቀዬዎቿ ነው።
የገጠሩ ኢትዮጵያ ትልቁ ምኞት ቀላል ነው። ከበሬው እስከ ገበሬው በሰላም ወጥቶ በሰላም የሚመለስበት፣ እርሻው በተስፋ የሚለማበት፣ የሕፃናት ሳቅ በቀዬው የሚያስተጋባበት አማን ሕይወት ማየት ነው።
ቀዬው ሰላም ሲሆን ምድሩ መልካም እሸት ያፈራል፤ ልቦች ይበልጥ ይቀራረባሉ፤ ሕይወትም ይለመልማል!
የኔ ኢትዮጵያ! ???????? ክፉው ሁሉ አይንካሽ፤ በጎውም አይለፍሽ! በእያንዳንዱ ቀዬሽ ሰላም ይስፈን፤ በእያንዳንዱ ቤት ተስፋ ይብቀል፤ በእያንዳንዱ በልጆችሽ ልብ አንድነት ይኑር። ያኔ እውነተኛ ውበትሽ በምልዐት ይገለጣል። የሰላም ብርሃንሽም ከቀዬ ወደ አደባባይ፤ ከገጠር ወደ ከተማው ከአንዱ ልብ ወደ ሌላው ይጋባል። በጽኑ አምናለሁ አይቀርም!
የሰላም ቀን ይሁንልን!
ሶዶ ለማ-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas
Published in
ህብረተሰብ

