Monday, 01 June 2026 07:02

"ምርጫው በሰላም እና በሥርዓት እየተካሄደ ነው” ኡሁሩ ኬንያታ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ መሪና የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ መጀመሩን ገልጸዋል።

በምርጫ ጣቢያዎች የተመለከቱት ነገር መልካም እንደነበር የጠቀሱት ኬንያታ፤ ይህ በሰላምና በሥርዓት የመምረጥ ሂደት ቀኑን ሙሉ እንዲቀጥል ተመኝተዋል።

“ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋና ከተማ ናት፤ በዚህች ሀገር የሚመዘገብ ስኬት ለመላው አህጉር ብርሃን ነው” በማለት ለኢትዮጵያ ሕዝብ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

Read 1321 times