Thursday, 21 May 2026 18:33

ግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ.ም በዛሬዋ_ዕለት

Written by 
Rate this item
(2 votes)
ከ35 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የቀድሞ (የኢ.ሕ.ድ.ሪ) ፕሬዝዳንት የኢትዮጵያ ህዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑሊክ፣ (የኢ.ሠ.ፓ) የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ ዋና ፀሐፊ የነበሩት ጓድ መንግስቱ ሃይለማርያም (ሌ/ኮ) ከአገር ወጥተው ወደ ሃገረ ዙምባቡዌ የሄዱበት ዕለት ነው።
ግንቦት 10 ቀን 1983 ዓ.ም ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማሪያም በመኖሪያ ቤታቸው ለከፍተኛ ባለስልጣኖቻቸው የእራት ግብዣ አደረጉ ፤ ግብዣው ሲጠናቀቅ ፕሬዘዳንቱ ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ ሁሉንም ተጋባዥ እንግዶች እበራፋቸው ላይ በመሆን አንድ ባንድ እየጨበጡ ሸኙዋቸው።
ግንቦት 12 ቀን 1983 ዓ.ም ፤ ፕሬዝዳንት መንግስቱ መሉውን ቀን የተለያዩ ወረቀቶችን እቢሯቸው ውስጥ ሲቀዳድዱ ዋሉ ፤ ማምሻው ላይ ግን ወደ ዘመቻ መምሪያ በማምራት ለከፍተኛ የጦር አዛዦቻቸው ንግግር አደረጉ።
ማክሰኛ ግንቦት 13 የፕሬዝዳንቱ ልዩ ረዳት ሻምበል መንግስቱ ፤ ብላቴ ማሰልጠኛ ጣቢያ ደርሶ ከዚያም ወደ አስመራ ደርሶ መልስ የሚበቃ ነዳጅ የሞላ አንድ ዳሽ 5 አውሮፕላን እንዲዘጋጅ ትእዛዝ አስተላለፉ።
በዛሬው እለት ከጠዋቱ ወደ 2:00 ገደማ ፕሬዝዳንቱ ከተመረጡ አጃቢዋች እንደዚሁም ከ3ኛው ክፍለጦር የመጣና የቅርብ አጃቢያቸው ከነበረው ከሻንበል ደመቀ ባንጃው ጋር በመሆን በኮሎኔል ተስፋዬ መሪነት ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በመድረስ ተዘጋጅታ ትጠብቅ ከነበረችው አውሮፕላን ተሳፈሩ።
©️ አብዮቱና ትዝታዬ (ሌፍተናንት ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ)
ታሪክን_ወደኋላ
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Read 10457 times