Thursday, 21 May 2026 18:17

ደቡብ አፍሪካ የኢቦላን ወረርሽኝ ለመግታት 2.5 ሚ. ዶላር አበረከተች

Written by 
Rate this item
(0 votes)
ደቡብ አፍሪካ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና በኡጋንዳ እየተከሰተ ያለውን የኢቦላ ወረርሽኝ ለመግታት ለሚደረገው ጥረት ድጋፍ የሚሆን 2.5 ሚሊዮን ዶላር ለአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማእከል የአፍሪካ ወረርሽኞች ፈንድ አበርክታለች። ይህ የተመደበው የገንዘብ ድጋፍ ሁለቱም ሀገራት ወረርሽኙን ለመዋጋት የሚያደርጉትን ቀጣይነት ያለው ትግል ለማገዝ፣ የአደጋ ጊዜ ምላሽ ስራዎችን ለማጠናከር፣ የበሽታ ቅኝትን ለማሳደግ እና የቀጣናውን ዝግጁነት ይበልጥ ለማገዝ የሚውል ነው።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Read 4514 times