ደቡብ አፍሪካ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና በኡጋንዳ እየተከሰተ ያለውን የኢቦላ ወረርሽኝ ለመግታት ለሚደረገው ጥረት ድጋፍ የሚሆን 2.5 ሚሊዮን ዶላር ለአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማእከል የአፍሪካ ወረርሽኞች ፈንድ አበርክታለች። ይህ የተመደበው የገንዘብ ድጋፍ ሁለቱም ሀገራት ወረርሽኙን ለመዋጋት የሚያደርጉትን ቀጣይነት ያለው ትግል ለማገዝ፣ የአደጋ ጊዜ ምላሽ ስራዎችን ለማጠናከር፣ የበሽታ ቅኝትን ለማሳደግ እና የቀጣናውን ዝግጁነት ይበልጥ ለማገዝ የሚውል ነው።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

