Tuesday, 19 May 2026 15:50

"ወህኒ አንባ" ታሪካዊ ቴአትር በታላቅ ድምቀት ሊመረቅ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)
በአዲስ አበባ ከተማ ለጥበብ አፍቃሪያን ታላቅ የምስራች ተሰምቷል። "ወህኒ አንባ" የተሰኘው አዲስ ታሪካዊ ቴአትር በመጪው እሁድ ግንቦት 16 ቀን በድምቀት ይመረቃል። ይህ በጉጉት የሚጠበቀው ታላቅ የጥበብ ስራ ፍላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው ዘመናዊው የህጻናት እና ወጣቶች አርት ኮምፕሌክስ መድረክ ላይ የሚቀርብ ሲሆን፤ በደራሲ መልካሙ ዘሪሁን ተፅፎ፣ በአዘጋጅ ዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ እና በረዳት አዘጋጅ ተስፋዬ ሲማ እጅግ ማራኪ በሆነ መልኩ ተዘጋጅቷል። ታዋቂ እና አንጋፋዎቹ የራስ ቴአትር ተዋናዮች የሚሳተፉበት በመሆኑ፣ ተዋናዮቹ የተለመደ ብቃታቸውን በተለየ ደረጃ ያሳዩበታል ተብሎ ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶታል።
በአሁኑ ወቅት የአዲስ አበባ የቴአትር ዘርፍ በከፍተኛ ሁኔታ እየተነቃቃ መሆኑን የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች እየገለጹ ይገኛሉ። የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደርም በቅርፅም ሆነ በይዘት ደረጃቸው እጅግ ከፍ ያሉ አዳዲስ ቴአትሮችን ወደ መድረክ እያመጣ በመሆኑ ትልቅ ምስጋና የተቸረው ሲሆን፣ የመገናኛ ብዙኀን ተቋማትም እነዚህን ስራዎች ለህዝብ በማስተዋወቅ ረገድ ላቅ ያለ ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Read 4468 times