Monday, 18 May 2026 17:31

ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን የሚቆጣጠር አዲስ ወታደራዊ አካል አቋቋመች

Written by 
Rate this item
(0 votes)
ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር እየበረታ የመጣውን ወታደራዊ ውጥረት ተከትሎ፣ ኢራን አለም አቀፍ የነዳጅ ቁልፍ መተላለፊያ በሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ ሙሉ ቁጥጥር የሚያደርግ አዲስ አካል ማቋቋሟን ይፋ አደረገች። የሀገሪቱ ከፍተኛ ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት እንደገለጸው፣ ይህ አዲስ ተቋም ከአሜሪካ የሚመጣውን ማንኛውንም አይነት ወታደራዊ ጫና ለመመከትና በአካባቢው ለሚነሱ እንቅስቃሴዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ታስቦ የተደራጀ ነው። በተጨማሪም የኢራን ፓርላማ በወሽመጡ በኩል ለሚያልፉ የባህር ትራፊኮች “ልዩ አገልግሎት” በሚል ክፍያ ለማስከፈል አዲስ አሰራር መዘርጋቱን አስታውቋል።
የሆርሙዝ ወሽመጥ የፋርስ ባህረ ሰላጤን ከኦማን ባህረ ሰላጤና ከዓለም ገበያ ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ፣ ለአለም አቀፉ የሃይልና የነዳጅ አቅርቦት ዋነኛ የልብ ትርታ ተደርጎ የሚወሰድ ስትራቴጂካዊ መስመር ነው። የአናዶሉ ኤጀንሲ እንደዘገበው፣ ኢራን የአዲሱን አካል ዝርዝር መዋቅርና ስልጣን በምስጢር ብትይዘውም፣ በአካባቢው የተደቀነው አለመረጋጋት በአለም አቀፉ የነዳጅና የጋዝ አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ስጋትና መስተጓጎል ሊፈጥር እንደሚችል ተገምቷል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Read 2260 times