ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳዋን ለመደገፍ ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ (AFD) 28.5 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ አገኘች። የድጋፍ ስምምነቱ 25 ሚሊዮን ዩሮ የበጀት ድጋፍና 3.5 ሚሊዮን ዩሮ የቴክኒክ ድጋፍን ያካትታል ተብሏል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ እንደገለጹት፤ ይህ ድጋፍ የኢትዮጵያን የመንግሥትና የግል ሽርክና፣ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ማሻሻያና የፋይናንስ ዘርፍ ተደራሽነትን ለማጠናከር ይረዳል። በተጨማሪም፤ ለውጤታማ ፖሊሲ ትግበራና ተቋማዊ አቅምን ለማሳደግ አስተዋፅኦ ያደርጋል ብለዋል።
የፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ (AFD) ዳይሬክተር ሚስተር ሉዊስ-አንቶይን ሶሼት በበኩላቸው፤ ኤጀንሲው የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ለውጥ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ድጋፍ አስተዳደርን፣ ኢኮኖሚያዊ ዘላቂነትንና የመንግሥት ዘርፍ ቅልጥፍናን ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
Wednesday, 02 April 2025 21:09
የፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ ለኢትዮጵያ የ28.5 ሚ. ዩሮ ድጋፍ አደረገ
Written by Administrator
Published in
ንግድና ኢኮኖሚ

