ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፣ በ3.6 ሚሊዮን ዶላር የገዛትን አዲስ ዘመናዊ አውሮፕላን ሰሞኑን በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተረክቧል፡፡ አውሮፕላኗ 14 ሰው የመያዝ አቅም ያላት ሲሆን፤ የተደራጀ የአውሮፕላን ማረፊያ በሌለባቸው ገጠራማ አካባቢዎች በቀላሉ ማረፍ እንደምትችልም የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እህት ኩባንያ የሆነው ትራንስ ኔሽንስ ኤር ዌይስ ሥራ አስኪያጅ፣ አቶ አሚር አብዱልወሃብ ለኢቢሲ ዶትስትሪም ተናግረዋል፡፡
“ሴስና ካራቫን ኤክስ” የሚል ስያሜ ያላት አዲሷ አውሮፕላን፤ ሚድሮክ በማዕድንና በእርሻ ዘርፍ የሚሰራቸው ሥራዎችን ለማሳለጥ ተጨማሪ አቅም እንደምትፈጥርም ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም አውሮፕላኗ ለጎብኚዎችና ለአገልግሎት ፈላጊዎች የቻርተር አገልግሎት እንደምትሰጥም ተናግረዋል፡፡
Published in
ንግድና ኢኮኖሚ

