Saturday, 25 May 2024 00:00

በኢትዮጵያ 8.8 ሚ. ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸው ተገለጸ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በተባበሩት መንግስታት፣ የሕጻናት አድን ድርጅት (ዩኒሴፍ)፤ በኢትዮጵያ 8.8 ሚሊዮን ሕጻናት ከትምሕርት ገበታ ውጭ ሆናቸውን አስታውቋል። ድርጅቱ ባለፈው ሰኞ ባወጣው የሩብ ዓመት ሪፖርት እንዳመለከተው፣ ከትምሕርት ገበታ ውጭ የሆኑ ሕጻናት ቁጥር በእጅጉ ጨምሯል።
በዩኒሴፍ የሩብ ዓመት ሪፖርት መሰረት፤ወደ 3 ሚሊዮን ለሚጠጉ ሕጻናት የትምህርት ድጋፍ ለማድረግ ጥረት ቢደረግም፣ ካለፈው ዓመት አጋማሽ አንስቶ ከትምህርት ውጭ የሆኑ ሕጻናት ቁጥር በከፍተኛ መጠን መደጉ ተመልክቷል፡፡
ባለፈው መጋቢት ወር ፣ 156 ሺ ያህል ሕጻናት ብቻ የድንገተኛ የትምህርት ድጋፍ እንዳገኙ የሚያትተው ሪፖርቱ፤ ለ ግሩመንስኤ ናቸው ያላቸውን ክስተቶች ዘርዝሯል። በስድስት ክልሎች የበልግ ወቅት ዝናብን ተከትሎ፣ በኢትዮጵያ 8.8 ሚ. ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸው ተገለጸ የተከሰቱ የጎርፍና በሰባት ክልሎች ያጋጠሙ የድርቅ አደጋዎች ለችግሩ መንስዔ እንደሆኑ
ተጠቁሟል፡፡ በፈረንጆቹ 2024 ዓ.ም የመጀመሪያ ሦስት ወራት ውስጥ የትምህርት መሰረተ ልማቶች ውድመት የ4 . 5 በመቶ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ በአገር አቀፍ ደረጃ የተዘጉ ት/ ቤቶች ብዛት በ18 በመቶ ማደጉን ሪፖርቱ ይጠቁማል፡፡በዚህ ሩብ ዓመት 21 ግብረ ሰናይ ድርጅቶች በቀውስ ለተጠቁ አካባቢዎች ድንገተኛ የትምህርት ድጋፍ ቢያደርጉም፣ ተጨማሪ
የድጋፍ ዓይነቶችና የሰብዓዊ ዕርዳታ እቅርቦት ከሌለ፣ አስከፊ ሁኔታ እየተፈጠረ ችግሩን ሊያሰፋው እንደሚችል ዩኒሴፍ ስጋቱን ገልጿል።
በኢትዮጵያ 10 ሚሊዮን ያህል ሕጻናት የትምህ ርት ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸውየዩኒሴፍ መረጃ ያሳያል።

Read 892 times