Saturday, 03 June 2023 20:08

14ኛው ከተማ አቀፍ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ‘’በሥነ ጥበባት ሕብራዊ መልክ የተዋበች ኢትዮጵያ’’ በሚል መርህ ከተማ አቀፍ  የኪነ ጥበብ ፌስቲቫል፣ ከነገ በስቲያ አርብ  ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት፣ በግዮን ሆቴል እንደሚካሄድ የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ፡፡  
የአዲስ አበባ ባህል፣ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ፣ የኪነጥበብ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሠርፀ ፍሬስብሃት፤ ቢሮው በከተማዋ ያለውን የኪነ-ጥበብ ሀብቶች  በዕይታዊና ክውን ጥበብ  አጉልቶ ለማሳየት የሚረዳ ዓመታዊ ትልቅ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫል በየዓመቱ በደማቅ ሁኔታ እንደሚያዘጋጅ ተናግረዋል።ቢሮው ለ14ኛ ጊዜ ባዘጋጀው ፌስቲቫል፤ የሥነ ጥበብ እንቅስቃሴዎችና ውድድሮች፣ ዐውደ ርዕይና ሥነ-ጥበባዊ ክዋኔዎች ይቀርባሉ ተብሏል።
 በፌስቲቫሉ ላይ በዕይታዊ ጥበባት፣ በክውን ጥበባት፣ በሥነ ፅሑፋዊ ጥበባት መስኮች ሥራዎች የሚቀርቡ ሲሆን በከተማዋ የሚገኙ የሥነ ጥበብ ተቋማት፣ ቴአትር ቤቶች፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሥነ ጥበብ ትምህርት ቤቶች፣የውጭ  ዲፕሎማቶች፣ የሀይማኖት  ተቋማት ፣ ከ11ዱም ከተማ የተወጣጡ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና የሙያ ማህበራት ይሳተፋሉ ተብሏል።

Read 740 times