Saturday, 03 June 2023 13:04

ራሚስ ባንክ በ2 ቢ. ብር የተፈረመ ካፒታል ሥራ ይጀምራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ራሚስ ባንክ፤ አስፈላጊውን የባንክ አደረጃጀትና መስፈርት አሟልቶና ከብሄራዊ ባንክ ፈቃድ አግኝቶ የተመሰረተ ሲሆን ፤የፊታችን እሁድ ግንቦት 27 ቀን 2015 ዓ.ም በዋና መሥሪያቤቱ   በይፋ ተመርቆ ስራ ይጀምራል።
 ባንኩ ከዛሬ ግንቦት 24 በኢሊሊ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፣ ይህን ያስታወቀው። ከመላው የሃገሪቱ ክፍሎት በተሰባሰቡ ከ8 ሺህ በላይ ባለአክሲዮኖች የተመሰረተው ባንኩ፤ በተፈረመ ከ2.1 ቢሊዮን ብር በላይና በተከፈለ ከ636 ሚሊዮን በላይ አጠቃላይ አደረጃጀቱን አጠናቅቆ፣ እሁድ ቦሌ መንገድ ፍላሚንጎ፣ ኦሮሚያ ፕሬዚዳንት ቢሮ ፊትለፊት በሚገኘውና ለዋና መስሪያ ቤትነት በገዛው ባለ ዘጠኝ ወለል ራሚስ ታወር ህንጻ ተመርቆ ስራ እንደሚጀምር ነው በመግለጫው የተነገረው፡፡
ባንኩ የስራውን ጅማሮ በአዲስ አበባ ዋናው መስሪያ ቤት አድርጎ፣በጥቂት ወራት ውስጥ የቅርንጫፎቹን ብዛት 50 ለማድረስ እየሰራ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነፃ አገልግሎት ለመስጠት የተደራጀው ባንኩ፤ በተለይም ለዚሁ አገልግሎት የሚያበቃውን አጠቃላይ ሂደት ጨርሶ ስራ ለመጀመር መቃረቡን የተናገሩት ሐላፊዎቹ፤ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙና ከወለድ ነፃ  የባንክ አገልግሎት  ከሚሰጡ ባንኮች አንዱና ቀዳሚው የመሆን ራዕይ ሰንቆ እየንቀሳቀሰ መሆኑም በጋዜጣዊ መግለጫው ተነግሯል።
ራሚስ ባንክ አክሲዮን ማህበር፣  ዘመኑን የሚዋጅና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት  የሚያስችለውን የኮር ባንኪንግ ሲስተም በማደራጀት ከሸሪአና  ፋይናንሺያል ደረጃ አደራጅቶ ስራ እንደሚጀምር አስታውቋል።በባንኩ የምርቃት ሰነስርዓት ላይ የብሄራዊ ባንክ ተወካዮች፣የተለያዩ የግል ባንክ ፕሬዚደንቶች ፣ከፍተኛ የመንግስት ሐላፊዎች፣  ጥሪ  የተረገላቸው እንግዶችና  ታዋቂ ሰዎች ይታደማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የባንኩ ሐላፊዎች ተናግረዋል።

Read 864 times