Saturday, 13 May 2023 20:07

ሥራ አስፈፃሚው በቢሯቸው ተገደሉ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አለባቸው አሞኜ በትላንትናው ዕለት በቢሯቸው ውስጥ መገደላቸው ተሰምቷል። ዋና ሥራ አስፈጻሚው በቢሯቸው ውስጥ ባለጉዳዮችን ተቀብለው በሚያነጋግሩበት ወቅት ባለጉዳይ ሆኖ ወደ ቢሮአቸው በገባ ሰው በተፈጸመባቸው ጥቃት ህይወታአው ማለፉ ነው የተነገረው። ግድያውን የፈጸመው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የካሳንቺስ አካባቢ ጣቢያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት የቀጠና ኦፊሰር እንደሆነና በቁጥጥር ስር መዋሉንና ምርመራ እያጣራ  እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።


Read 1667 times