Saturday, 28 January 2023 21:18

“ያውዌ” የሙዚቃ ኮንሰርት ጥር 27 በግሮቭ ጋርደን ዎክ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(2 votes)

 “ያውዌ” የተሰኘ መጠሪያ ያለው የሙዚቃ ኮንሰርት ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም ጊዮን ሆቴል ውስጥ በሚገኘው ግሮቭ ጋርደን ዎክ ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡ በእለቱም በጉራጊኛ ድምፃዊነታቸው ተወዳጅነትን ያተረፉት ድምፃዊያን ሀና ተሰማ(ያውዌ) ፣ ደምሴ ተካ፣ ፀጋዬ ስሜ (ሆሴ ባሳ)፣ ሀይሉ ፈረጃ ፣ ደሳለኝ መርሻ፣ ፈለቀ ማሩ ፣ አምደ ገብርኤል አድማሱ ፣ ግዛቸው ተሸመና የባህል ድምፃዊው ደመረ ለገሰ ፣ ስዩም ጥላሁን (አንቺ ወረተኛ)እና ሌሎችም ተወዳጅ ድምፃዊያን ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
የመግቢያ ዋጋው መደበኛው 500 ብር ቪአይፒው 1000 ብር ሲሆን ሁሉም በቴሌ ብር በኩል እንደሚገኙ የኮንሰርቱ አዘጋጅ “መደሰቻ” መልቲ ሚዲያ አስታውቋል፡፡

Read 9049 times