በዳንኤል ዓለሙ (የምህረት ልጅ) የተዘጋጀው “ራስን የመለወጥ ምስጢር” የፍልስፍናን እና የሥነልቦና መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ መጽሐፉ ራስን ስለመግዛት፣ እውነተኛ ስለመሆን እና በታማኝነት ስለመኖር የተዘጋጁ ጽሑፎች ቀርበውበታል፡፡ 64 ገጽ ያለው መጽሐፍ በ18 ብር እየተሸጠ ነው፡፡ ዳንኤል ካሁን ቀደም “ፈተናን የማሸነፍ ጥበብ” ፣ “ስኬታማ የፍቅር ሕይወት”፣ “ገንዘብ እና ጭንቀት” እና “ራስን የመለወጥ ምስጢር” የሚሉ መፃሕፍት ለንባብ አብቅቷል፡፡