አለልኝ መኳንንት ጽጌ ጽፎ ያዘጋጀው “የፍቅር ካቴና” ቴአትር ማክሰኞ ከቀኑ 10፡30 እንደሚመረቅ አዘጋጅቼ “አፍሪካ ቴአትር ሚዲያ” አስታወቀ፡፡ ቴአትሩ የሚመረቀው በሐገር ፍቅር ቴአትር ነው፡፡
ትያትሩ ከተፃፈ ሶስት ዓመት ቢያልፈውም በትያትር ቤቶች የወረፋና የግምገማ ሂደት መራዘም አሁን ገና ለእይታ መብቃቱንና በእነዚህ አመታት አራት ጊዜ መገምገሙን አለልኝ ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡ በኮሜዲ ትያትሩ ሃና ተረፈ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ወይንሸት አበጀ እና አሸናፊ ማህሌት ይተውናሉ፡፡ ደራሲና አዘጋጁ በኢትዮጵያ ቴሌቭዢን ያቀርባቸው በነበሩት የቴሌቭዢን ድራማዎች ፀሐፊና አዘጋጅነቱ ይታወቃል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና