Print this page
Saturday, 14 January 2023 10:41

“አሳንቲ” ዛሬ በሐገር ፍቅር ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(4 votes)

   የደራሲ  ምርት ባቦ የበኩር ሥራ የሆነው “አሳንቲ “ የተሰኘ የአጫጭር ልብወለዶች መድበል ዛሬ  ቅዳሜ ከጠዋቱ 4 ሰዓት በሐገር ፍቅር ቴአትር ቤት እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡
በ212 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ አምስት አጫጭር ልብወለድ ታሪኮችን ያካተተ ነው፡፡
 በምርቃት  ፕሮግራሙ ላይ ሥራዎቻቸውን ከሚያቀርቡ  ታዋቂ የሥነጽሁፍ  ባለሙያዎች መካከል  ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ ደራሲ ዘነበ ወላ፣ የህግ ባለሙያው ተክለሚካኤል አበበ፣ ገጣሚ  ሰለሞን ሳህለ፣ ተዋናይ ፍቃዱ ከበደና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡
የምርቃት ፕሮግራሙን  ኒው አቢሲኒያ ባንድ በሙዚቃ  እንደሚያደምቀው ታውቋል፡፡

Read 1641 times
Administrator

Latest from Administrator