የደራሲ ምርት ባቦ የበኩር ሥራ የሆነው “አሳንቲ “ የተሰኘ የአጫጭር ልብወለዶች መድበል ዛሬ ቅዳሜ ከጠዋቱ 4 ሰዓት በሐገር ፍቅር ቴአትር ቤት እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡
በ212 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ አምስት አጫጭር ልብወለድ ታሪኮችን ያካተተ ነው፡፡
በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ ሥራዎቻቸውን ከሚያቀርቡ ታዋቂ የሥነጽሁፍ ባለሙያዎች መካከል ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ ደራሲ ዘነበ ወላ፣ የህግ ባለሙያው ተክለሚካኤል አበበ፣ ገጣሚ ሰለሞን ሳህለ፣ ተዋናይ ፍቃዱ ከበደና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡
የምርቃት ፕሮግራሙን ኒው አቢሲኒያ ባንድ በሙዚቃ እንደሚያደምቀው ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና