በመንግስት ምህሪት ከእስር ተለቀው የነበሩት የህውሃት መሥራችና አመራሩ አቶ ስብሐት ነጋ ለህክምና ወደ ውጪ አገር እንዳልሄድ ከህግ ውጪ በፌደራል ፖሊስ ተከለከልኩ ሲሉ ክስ አቀረቡ።
አቶ ስብሐት ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ መሰረታዊ መብቶች ጉዳዮች ችሎት ትናንት ባቀረቡት ክስ እንዳመለከቱት፤ “ለህክምና ወደ ውጪ አገር እንዳልሄድ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ ከቦሌ አየር ማረፊያ እንድመለስ ተደርጌአለሁ” ብለዋል። አቶ ስብሐት ነጋ በጠበቃቸው አማካኝንነት ባቀረቡት ክስ ላይ እንዳመለከቱት፤ አገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ የፈረመቻቸውን ህጎች ባልተከተለና በህገ-መንግስቱ የተቀመጠውን የዜጎችን በነፃነት መንቀሳቀስ መብት በሚጋፉ መልኩ ፍርድ ቤት ሳያዝ ፖሊስ ከስልጣኑ ውጪ የጉዞ እገዳ እንደጣለባቸው ተጠቁሟል።
የአቶ ስብሐት ነጋን ክስ የተቀብለው ፍ/ቤቱ፤ በጉዳዩ ዙሪያ ፖሊስ መልስ ባለማቅረቡ ሳቢያ መልስ የመስጠት መብቱ እንዲታለፍ ብይን ሰጥቷል። በጉዳዩ ላይ ውሳኔ ለመስጠትም ለመጪው ረቡዕ ቀጠሮ ሰጥቷል።
አቶ ስብሐት ነጋ "ወደ ውጪ አገር እንዳልወጣ ታገድኩ” ሲሉ ፖሊስን ከሰሱ
Written by AdministratorLatest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል