Saturday, 26 November 2022 00:00

ደብዳቤ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ከዳግማዊ ምኒልክ ለፕሬዚዳንት ሩዝቬልት የተጻፈ ደብዳቤ

      ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ ዳግማዊ ምኒልክ ስዩመ እግዚአብሔር፣ ንጉሠ-ነገሥት ዘኢትዮጵያ።
ይድረስ ለክቡር የዩናይትድ እስቴት መንግሥት ፕሬዚዳንት ሮዝቤል።
ሰላም ለእርስዎ ይሁን።
ባለሙሉ ስልጣን ሆኖ ለመጣው መልክተኛዎ ቆንስል ጀነራል እስኪነር የላኩት ደብዳቤ ደርሶኛል። እስካሁን በኔና በርስዎ መንግስት የፍቅር መላላክ አልነበረም እንጂ ከጥንት የሁለታችን አገር ነጋዴዎች እየተመላለሱ ይነግዱ ነበር። በፍቅርና በንግድ ውል ከተስማማን፣ የሁለታችን መንግስት ፍቅራችን እየበረታ ለዘላለም እንዲኖር ተስፋ አለን። ፎቶግራፍዎና ካገርዎ አዲስ የተሰራ ጠበንጃ፣ የጽፈት መኪና ደርሶኛል።
እግዚአብሔር ይስጥልኝ። እኔም አዲስ ስለተጀመረው ፍቅራችን መታሰቢያ ሁለት የዝሆን ጥርስ፣ ሁለት አንበሶች ልኬአለሁ። ይህን ጥቂቱን ስለብዙ አድርገው ይቀበሉኝ። እርስዎንና የዩናይትድ እስቴት መንግሥት ሕዝብን እንዲጠብቅ እግዚአብሔርን እለምናሁ።
ታህሳስ 17 ቀን 1896 ዓመተ ምሕረት አዲስ አበባ ከተማ ተፃፈ።

Read 1308 times