Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 27 October 2012 09:33

የቴዲ አፍሮ የሐዋሳ ኮንሰርት ለሳምንት ተላለፈ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ስቴዲየሙ ለጨዋታ ተፈልጓል
በዛሬው ዕለት በሐዋሳ ከተማ ሊደረግ ታቅዶ የነበረው የአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የሙዚቃ ኮንሰርት ስቴዲየሙ ለኳስ ጨዋታ በመፈለጉ ተሰርዞ ለሚቀጥለው ቅዳሜ ተላለፈ፡፡ የቤለማ ኢንተርቴይመንት የፕሮሞሽን እና ኢቬንት ሐላፊ አቶ ምኞት ኃይሉ (ዲጄ ዊሽ) ለአዲስ አድማስ እንደገለፀው፤ ቤለማ ኢንተርቴይመንት በዛሬው ዕለት በሐዋሳ ከተማ ትልቅ የሙዚቃ ዝግጅት ለማቅረብ አስቦ ዝግጅቱን ካጠናቀቀ በኋላ ኮንሰርቱ ሊደረግበት የታቀደው ስታዲየም ለኳስ ጨዋታ ይፈለጋል በመባሉ ዝግጅቱ ለጥቅምት 24 ቀን 2005 ዓ.ም ሊተላለፍ ችሏል፡፡

ዝግጅቱ በዕለቱ ሊደረግ ከታቀደ በኋላ ለፕሪሚየር ሊግ ዕጣ ሲወጣ የሐዋሳ ከነማ እና የመድሕን ጨዋታ ጥቅምት 17 ቀን 2004 ዓ.ም በሐዋሳ ስታዲየም ስለወጣላቸው ኮንሰርቱ ሊተላለፍ እንደቻለ ታውቋል፡፡ 
የዝግጅቱ ቀን በመተላለፉ ለማስታወቂያ ከወጣው 42 ሺህ ብር ውጭ ምንም ዓይነት ኪሣራ አለመድረሱን የገለፀው ዲጄ ዊሽ፤ በቀኑ መተላለፍ ምክንያት ተፈጥሮ የነበረው ትልቅ ስጋት የአርቲስት ቴዲ አፍሮን ፕሮግራም አለማወቃቸው መሆኑን ጠቁሞ፤ ሆኖም አርቲስቱ እና ዛየን ባንድ ትልቅ ትብብር እንዳደረጉላቸው ገልጿል፡፡

Read 2627 times