Print this page
Sunday, 06 November 2022 18:32

ክቡር ዶ/ር አሊ ቢራ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

Written by 
Rate this item
(15 votes)

 ታዋቂው የኦሮምኛ ዜማ አቀንቃኙ ክቡር ዶክተር ዓሊ ቢራ ባደረበት ህመም ህክምና ሲከታተል ቆይቶ፣ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡

 ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት፤"የአንጋፋው ድምጻዊ ዓሊ ቢራ ኅልፈት ለኢትዮጵያ ጉዳት ነው። በዜማዎቹ ኅብረትን፣ ጽናትንና ባህልን አቀንቅኗል። ለብዙዎችም አርአያ ሆኗል። ላደረከው ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግንሃለች።" ብለዋል፡፡

 አርቲስት ዓሊ ቢራ በ1954 ዓ.ም የኦሮምኛ ሙዚቃን ለማስተዋወቅ ዓላማ ያደረገ የባህላዊ ሙዚቃ ቡድን “አፍረን ቀሎ”ን በመቀላቀል ነበር፣ የሙዚቃ ስራውን የጀመረው። አርቲስቱ ከኦሮምኛ በተጨማሪ፣ በሶማሊኛ፣ አፋርኛ፡ ሐረሪ፣ አማርኛና አረብኛ ቋንቋዎች በርካታ ዘፈኖችን ተጫውቷል።

 ዝግጅት ክፍሉ በክቡር ዶክተር አሊ ቢራ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለጸ፤ፈጣሪ ለቤተሰቦቹ ወዳጆቹና አድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡

Read 20971 times
Administrator

Latest from Administrator